- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

ከአድማስ ወዲህ፡ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዐቢዮት በኢትዮጵያ

ከአድማስ ወዲህ፡ የሠው ሠራሽ አስተውሎት ዐቢዮት በኢትዮጵያ
ሰብስክራይብ

''የሰው ሰራሽ አስተውሎት በመላው ዓለም ምጣኔ ሐብን እየለወጠ ይገኛል። በዚህ ረገድ ከሌላው ሀገር ወደኃላ መቅረት የለብንም — እንደሚታወቀው ሠው ሰራሽ አስተውሎት የዲጂታል ኢኮኖሚ ላይ ተፅዕኖ አለው። ስለዚህ እንደ አፍሪካ ኅብረት አባልነታችን በአህጉር ደረጃ በርካታ ሥራዎችን እየሰራን ነው ፡፡ '' ሲሉ በባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ተቋም የኮምፒቲሽናል ሳይንስ እና የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዳይሬክተሩ ዮናስ ገ/ሚካኤል ድፈር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ሶቨርኒቲ ሶርስስ በዛሬው መርሃ ግብሩ በክፍል አንድ የሠው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂን ፈር ለማስያዝ እንዲሁም ፈጣራን ለማበረታታት ስለሚጫወተው ቁልፍ ሚና ለመወያየት በባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ተቋም የኮምፒቲሽናል ሳይንስ እና የሠው ሠራሽ አስተውህሎት ዳይሬክተሩ ዮናስ ገ/ሚካኤል ድፈርን በእንግድነት ጋብዘናቸዋል።

የማቴሪያል ሳይንስ ኢንጂነሪንግ የሀይል አጠቃቀምን ለመቀነስ፣ ተግዳሮቶቹን እዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን ጉዳይን ተደራሽ ለማድረግ ስለሚፈጥረው አቅም ከኬሚስቱና ተመራማሪው ዶ/ር መላኩ ደረጄ ጋር የተደረገው ቆይታም ሌላኛው ጉዳያችን ነው።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0