- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

አፈወርቅ ተክሌ ፡- የአፍሪካ ታሪክ ፣ ኃይል እና ኩራት ሰዓሊ

አፈወርቅ ተክሌ፡- የአፍሪካ ታሪክ ፣ ኃይል እና ኩራት ሰዓሊ
ሰብስክራይብ

''የሀገሩን ባህል፣ ታሪክና ልማድ ጠንቅቆ የሚያውቅ ታላቅ ሰዓሊ ነበር — ስብዕናውን ከኢትዮጵያ ጋር ከነበረው ቁርኝት ነጥሎ ማየት ከባድ ነው -'' ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አለ ት/ቤት የፋይን አርትስና ዲዛይን መምህር ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ሶቨርኒቲ ሶርስስ በዛሬው መርሃ ግብሩ በክፍል አንድ ፡ እጅግ የተከበሩ የዓለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ለዘመናት የተሻገረውን የኪነ ጥበብ አሻራ፣ ማንነትና አፍሪካዊ ትርክትን ለመወያየት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አለ ት/ቤት የፋይን አርትስና ዲዛይን መምህር ፕሮፌሰር በቀለ መኮንን በእንግድነት ጋብዟቸዋል። አፍሪካ በዓለም አቀፍ መድረክ ተፅዕኖን ለመፍጠር ራሷን ስለመቻል እንዲሁም የጎለበተ ዲፕሎማሲ መፍጠር በተመለከተ የሆርን ሪቪው ዳይሬክተርና በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ተመራማሪ ብሌን ማሞ ጋር የተደረገው ቆይታም ሌላኛው ጉዳያችን ነው።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0