ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በጥቂት እጅ ጠምዛዥ ኃያላን ሀገራት ሥር ነው - የቱርክ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ዳኛ

ሰብስክራይብ

ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በጥቂት እጅ ጠምዛዥ ኃያላን ሀገራት ሥር ነው - የቱርክ ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ዳኛ

ኢንጂን ይልዲሪም (ፕ/ር)፤ ፍርድ ቤቱ በእኚህ ኃያላን አገራት በሚደርስበት ጫና ሳቢያ ደካሞችን እየመረጠ ወደመቅጣት መውረዱን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"ለምሳሌ ጋዛ ውስጥ በእስራኤል መንግሥት የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል። ፍርድ ቤቱ በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ የእስር ትዕዛዝ ቢያወጣም ማንም ጉዳዬ ብሎ አልያዘውም። የፍርድ ቤቱ ሥልጣን የሚታየው በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገራት ላይ ነው" ብለዋል።

ዳኛው ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ለኢ-ፍትሐዊነት የዳረገውን የጣምራ ሚዛን አሠራር ማረም እንዳለበትም አመላክተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0