የሱዳን ጦር በደቡብ ኮርዶፋን በርካታ መንደሮችን መልሶ ተቆጣጠረ

ሰብስክራይብ

የሱዳን ጦር በደቡብ ኮርዶፋን በርካታ መንደሮችን መልሶ ተቆጣጠረ

በመንግሥት ኃይሎች ቁጥጥር ስር የገቡት ሰባቱ መንደሮች እና ትናንሽ ከተሞች እ.አ.አ ከ2011 ጀምሮ በደቡብ ኮርዶፋን እና በብሉ ናይል ግዛቶች የራስ ገዝ አስተዳደር ለማግኘት ሲዋጋ በነበረው የሱዳን ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ-ሰሜን ቁጥጥር ስር እንደነበሩ የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ይህ በሀገሪቱ በሚያዝያ 2023 ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ ጦሩ በአካባቢው ያደረገው የመጀመሪያው ትልቅ ጥቃት እንደሆነ ተዘግቧል።

በባለሙያዎች ግምት መሰረት፤ በመደበኛው የሱዳን ጦር እና በኢ-መደበኛው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል መካከል የተፈጠረው የእርስ በርስ ግጭት ቢያንስ 40 ሺህ ሰዎችን ለሞት ዳርጓል። ወደ 14 ሚሊዮን የሚጠጉ ሱዳናውያን ቤታቸውን ጥለው ለመሸሽ ተገደዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0