አፍሪካ ለሁለት ትከፈላለች፤ አሁን እየታዩ ያሉት ክስተቶችም የረጅም ጊዜ ሂደት ምልክቶች ናቸው - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአፍሪካ ለሁለት ትከፈላለች፤ አሁን እየታዩ ያሉት ክስተቶችም የረጅም ጊዜ ሂደት ምልክቶች ናቸው - ባለሙያ
አፍሪካ ለሁለት ትከፈላለች፤ አሁን እየታዩ ያሉት ክስተቶችም የረጅም ጊዜ ሂደት ምልክቶች ናቸው - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.12.2025
ሰብስክራይብ

አፍሪካ ለሁለት ትከፈላለች፤ አሁን እየታዩ ያሉት ክስተቶችም የረጅም ጊዜ ሂደት ምልክቶች ናቸው - ባለሙያ

“በአፍሪካ ኑቢያን የመሬት ክፍል፣ የምዕራብ እና ሰሜናዊ አፍሪካን የሚያካትት ሲሆን ወደ ምዕራብ እየተጓዘ ነው፡፡ ምስራቃዊ አፍሪካን፣ ኢትዮጵያን፣ ኬንያን፣ ታንዛኒያን እና ሶማሊያን የሚያካትተው እና የሶማሊያ የመሬት ክፍል ተብሎ የሚጠራው ወደ ምስራቅ እየተጓዘ ነው፡፡ አሁን ላይ እነዚህ አካባቢዎች በንቃት እየተለጠጡ ነው” ሲሉ የማዕድን ዘርፍ አማካሪው ሙስጠፋ ሻይቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

የምድር ቅርፊት እየቀጠነ፣ ጥልቅ ሸለቆዎች እየተፈጠሩ፣ የእሳተ ገሞራ እንቅስቃሴዎች እየታዩ እና የመሬት መንቀጥቀጦች እየደረሱ መሆናቸው የረዥም ግዜ ሂደቱ ምልክቶቹ ናቸው ሱሉ ባለሙያው አስረድተዋል፡፡

ሁሉም ሂደት ቅጽበታዊ ሳይሆን የዝግመተ ለውጥ ውጤት ነው የሚሉት ባለሙያው፤ የምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ እየሰፋ ሲሄድ አዲስ ውቅያኖስ ይፈጠራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡

“ከጊዜ ወደ ጊዜ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አናውቅም። እነዚህ ሂደቶች እየተከሰቱ ቢሆንም፣ ወዲያውኑ እና በአጭር ጊዜ የሚፈጸም ሂደት አይደለም፡፡ ነገ ይሆናል ማለት አይቻልም። ይህ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ዓመታት የሚቆይ የዝግመተ ለውጥ ሂደት ነው፡፡ አሁን እንደተጀመረው ሁሉ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ በተመሳሳይ መልኩ፣ ምናልባትም በትላልቅ እና ሰፋ ባሉ መጠኖች ሂደቶችን ማየት እንችላለን” ብለዋል፡፡

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0