የጊኒ-ቢሳው ወታደራዊ አገዛዝ የሀገሪቱን አንጋፋ ፓርቲ መሪ መልቀቃቸው ተዘገበ
19:35 01.12.2025 (የተሻሻለ: 19:44 01.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጊኒ-ቢሳው ወታደራዊ አገዛዝ የሀገሪቱን አንጋፋ ፓርቲ መሪ መልቀቃቸው ተዘገበ
ለጊኒ እና ኬፕ ቨርዴ ነፃነት የአፍሪካ ፓርቲ አባል የሆኑት ዶሚንጎስ ፔሬራ፤ ከሌሎች ታዋቂ ፖለቲከኞች ጋር ህዳር 17 ከተካሄደው ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት በኋላ ከኦስቫልዶ ቪየራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ ተይዘው ነበር።
◻ በሕዝባዊ ግንባር ስር የተሰባሰቡ የተቃዋሚ ድርጅቶች ዶሚንጎስ ፔሬራ እንዲለቀቁ በመጠየቅ የጊኒ-ቢሳው ሕዝብ የሲቪል እምቢተኝነት እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል። ኢኮዋስ እና የአፍሪካ ኅብረት ይህን ጥሪ ተቀላቅለዋል።
ህዳር 14 የተካሄደው የጊኒ-ቢሳው ፕሬዝዳንታዊ እና የፓርላማ ምርጫ ውጤት ከመገለጹ በፊት ህዳር 17 ቀን ወታደሮች ፕሬዝዳንት ኡማሮ ሲሶኮ ኤምባሎን በመፈንቅለ መንግሥት በማንሳት ሥልጣን ይዘዋል።
◻ ሁሉንም የመንግሥት ተቋማት ማገዳቸውን እና ሥርዓት ለመመለስ ሥልጣን ለከፍተኛ ወታደራዊ ኃይል ዕዝ ማስተላለፋቸውን አስታውቀዋል። ሜጀር ጄኔራል ሆርታ ኢንታ-አ ህዳር 18 ቀን የሽግግር ግዜ ፕሬዝዳንት ሆነው ሥልጣን ጨብጠዋል።
ወታደሮች የምርጫ ድምጽ ቆጠራ እንዲቆም አዘዋል። እጩነታቸው ከምርጫው በፊት የተሰረዘው ፔሬራን ጨምሮ በርካታ ፖለቲከኞችም ታስረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X