ኢትዮጵያ የሳታላይት ዳታን ያለማቋረጥ የሚቀበል ቴክኖሎጂ አስጀመረች
19:24 01.12.2025 (የተሻሻለ: 13:54 02.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የሳታላይት ዳታን ያለማቋረጥ የሚቀበል ቴክኖሎጂ አስጀመረች
ቴክኖሎጂው በቋሚነት መሬት ላይ የሚተከልና የአንድን ቦታ መገኛ ከጂ.ፒ.ኤስ በመቀበል ከፍተኛ ጥራት ያለው መረጃ የሚሰጥ መሆኑን የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ ተናግረዋል፡፡
“ይህ የቦታ አሁናዊ መገኛ አመልካች ቴክኖሎጂ የቅየሳ ሞያተኞች፣ ተመራማሪዎች፣ የአደጋ ተንታኞች፣ የመልክዓምድር እና የልዩ አገልግሎት ካርታ የሚያዘጋጁ ሞያተኞች ሥራ በሚሠሩበት ወቅት የያዙት ተንቀሳቃሽ የጂ.ፒ.ኤስ መሳሪያ የቆሙበት ቦታ መገኛን በሳንቲ ሜትር ደረጃ መረጃ የሚሰጥ ነው” ሲሉ ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
የቴክኖሎጂው ተጨማሪ አገልግሎቶች፦
ግድቦችን መገንባትና ደህንነታቸውን መከታተል፣
የመሬት አስተዳደር አሠራርን ማሻሻል፤
የሎጂስቲክስ ስርዓቱን ማሳለጥ፣
ልዩ ልዩ መሠረተልማቶችን ማስፋፋት፣
ግብርናንና የማዕድን ዘርፉን ማዘመን፡፡
ቴክኖሎጂው የቅየሳ ሥራ ለመሥራት መነሻ የሚሆኑ ተጨማሪ የጂ.ፒ.ኤስ መሳሪያዎች መትከል የግድ የነበረውን አሠራር ያስቀረ ነው ተብሏል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X