ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ሃያላን ሀገራትን ለፍትሕ የማቅረብ አቅም የለውም - የሕግ ምሑር

ሰብስክራይብ

ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ሃያላን ሀገራትን ለፍትሕ የማቅረብ አቅም የለውም - የሕግ ምሑር

ፍርድ ቤቱ በምዕራቡ ዓለም የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ከማየት ይልቅ በአፍሪካ ሀገራት ጉዳዮች መጠመዱን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሕግ ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር ጌታቸው አሰፋ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"በአብዛኛው በፍርድ ቤቱ እየተከሰሱ ያሉት በአፍሪካ የሚገኙ መሪዎች እና ቡድኖች ናቸው። ከአፍሪካ ውጭ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን እንዳላየ የማለፍ ልምምዱ የሚያሳይህ ፍርድ ቤቱ በሁሉም ሀገራት ላይ እኩል ኃይል እንደሌለው ነው" ብለዋል።

ምሑሩ ፍርድ ቤቱ ወንጀል እና ወንጀለኞችን በጡንቻ ከመመዘን ይልቅ ለፍትሕ እና ለመርሕ ሊሠራ እንደሚገባም አጽዕኖት ሰጥተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0