ዳንጎቴ ከታህሳስ 2025 ጀምሮ ለናይጄሪያውያን በየወሩ የተረጋጋ 1.5 ቢሊዮን ሊትር ቤንዚን ለማቅረብ ቃል ገባ
13:59 01.12.2025 (የተሻሻለ: 14:04 01.12.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዳንጎቴ ከታህሳስ 2025 ጀምሮ ለናይጄሪያውያን በየወሩ የተረጋጋ 1.5 ቢሊዮን ሊትር ቤንዚን ለማቅረብ ቃል ገባ
ኩባንያው ከታህሳስ 2025 እስከ ጥር 2026 በቀን 50 ሚሊዮን ሊትር እንደሚያቀርብ፤ ከየካቲት 2026 ጀምሮ ደግሞ አቅርቦቱን በቀን ወደ 57 ሚሊዮን ሊትር እንደሚያሳድግ በመግለጫው አስታውቋል።
ሙሉ ግልጽነኝነትን ለማስጠበቅ ቁርጠኛ መሆኑን የገለጸው ዳንጎቴ፤ የዕለት ምርቱን እና የክምችት መጠኑን በኦንላይን እና በህትመት ሚዲያዎች ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ ብሏል።
በተጨማሪም የናይጄሪያ የመካከለኛ ዘርፍ የነዳጅ ቁጥጥር ባለሥልጣን ጥሬ እቃዎችን፣ ግብዓቶችን እና ውህድ ክፍሎችን ያለእንቅፋት ማስገባቱን እንዲደግፍ ጠይቋል።
"የናይጄሪያን የሀገር ውስጥ ነዳጅ ደህንነት እና ሰፊ አቅርቦት ለማረጋገጥ የተለመደ ትኩረት እና ድጋፋችሁን እናደንቃለን። የ 'ናይጄሪያ ቅድሚያ' ፖሊሲ ለሁሉም ናይጄሪያውያን ጥቅም እንዲሠራ እንጠይቃለን" ሲልም በመግለጫው ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X