የዩክሬን ፀረ-ሙስና ቢሮ በዘለንስኪ ፓርቲ የምክር ቤት አባላት ላይ ክስ ለመመስረት እየተዘጋጀ መሆኑን ሕግ አውጪው ተናገሩ
19:11 30.11.2025 (የተሻሻለ: 19:14 30.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የዩክሬን ፀረ-ሙስና ቢሮ በዘለንስኪ ፓርቲ የምክር ቤት አባላት ላይ ክስ ለመመስረት እየተዘጋጀ መሆኑን ሕግ አውጪው ተናገሩ
በርካታ የዘለንስኪ “የሕዝብ አገልጋይ” ፓርቲ አባላት በቅርቡ በሕገ-ወጥ ገንዘብ ዝውውር እና ሕገ-ወጥ ጥቅም የማግኘት ሴራ ክስ እንደሚጠብቃቸው፤ በሀገር ክህደት ክስ ተይዘው የሚገኙት የምክር ቤት አባል ኦሌክሳንደር ዱቢንስኪ በቴሌግራም ባሰፈሩት ፅሑፍ ገልፀዋል።
ዜናው የብሔራዊ ፀረ-ሙስና ቢሮ በዩክሬን የኃይል ዘርፍ እያካሄደ ያለውን የፀረ-ሙስና ዘመቻ ተከትሎ የመጣ ሲሆን ቢሮው በቅርቡ ባደረጋቸው ፍተሻዎች በውጭ ምንዛሪ የተሞሉ ሻንጣዎችን በመያዝ ፎቶግራፎችን ይፋ አድርጓል።
ምርመራው የቀድሞው የፕሬዝዳንት ፅሕፈት ቤት ኃላፊ አንድሪ የርማክን፣ የቀድሞው የኃይል ሚኒስትር ሄርማን ጋሉሽቼንኮን እና የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሌክሲ ቼርኒሾቭን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ተጠያቂ አድርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X