ካዛክስታን ዩክሬን በወሳኝ የነዳጅ ጣቢያ ላይ የፈፀመችውን የድሮን ጥቃት ኮነነች
16:29 30.11.2025 (የተሻሻለ: 16:34 30.11.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ካዛክስታን ዩክሬን በወሳኝ የነዳጅ ጣቢያ ላይ የፈፀመችውን የድሮን ጥቃት ኮነነች
አስታና በኪዬቭ አስተዳደር ላይ ያቀረበችው ይፋዊ ተቃውሞ ዩክሬን በሩሲያ ኖቮሮሲስክ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው "የካስፒያን ፓይፕላይን ኮንሰርቲየም" (ሲፒሲ) የባሕር ጣቢያ ላይ በሌሊት የፈፀመችው የድሮን ጥቃት ከባድ ጉዳት ካደረሠ በኋላ የመጣ ነው። ጥቃቱ ቁልፍ መጫኛው አገልግሎት እንዳይሰጥ አድርጓል።
የካዛክስታን መንግሥት ድርጊቱን “ለሁለትዮሽ ግንኙነት ጎጂ” ሲል በማውገዝ፤ መሠረታዊ በሆኑ የሲቪል መሠረተ ልማቶች ላይ ተጨማሪ ጥቃቶች እንዳይደርሱ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ጠይቋል።
የዩክሬን ኃይሎች የሲፒሲን ተቋማት ዒላማ ሲያደርጉ በዚህ ዓመት ለሶስተኛ ጊዜ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X