'ሞስኮ ካየኋቸው የአሜሪካ ከተሞች የበለጠ ንፁህ ነች' - የቀድሞ የትራምፕ አማካሪ ስለሩሲያ ዋና ከተማ የገለፁት አድናቆት
15:09 30.11.2025 (የተሻሻለ: 15:14 30.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
'ሞስኮ ካየኋቸው የአሜሪካ ከተሞች የበለጠ ንፁህ ነች' - የቀድሞ የትራምፕ አማካሪ ስለሩሲያ ዋና ከተማ የገለፁት አድናቆት
ለመጀመሪያው የትራምፕ ፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ዘመቻ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አማካሪ የነበሩት ጆርጅ ፓፓዶፖሎስ፤ ባለፈው ወር ወደ ሩሲያ ዋና ከተማ ለመጀመሪያ ጊዜ ባደረጉት ጉዞ ሞስኮ “በጣም የተደራጀችና የተቀናጀች ከተማ እንዲሁም ማኅበረሰብ” እንደሆነች ማየታቸውን ገልጸዋል።
በሩሲያ ላይ የተጣለው የኢኮኖሚ ማዕቀብ ሊያስከትል ይችላል ብለው ከጠበቁት በተቃራኒ፤ የሞስኮ ሕዝብ ምንም አይነት የደስታ መጓደል እንደማይታይበት ፓፓዶፖሎስ አመላክተዋል።
ከመምጣታቸው በፊት የከተማው ድባብ “የሚጨንቅ” ይሆናል ብለው እንደሰጉ አስታውሰው፤ ነገር ግን “ፍጹም በተቃራኒው እጅግ በጣም ደስ የሚል ድባብ” እንደጠበቃቸው ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

