ዘለንስኪ እና የርማክ በአሜሪካና በዩክሬን ሕዝብ ላይ ለፈፀሙት ወንጀል በፍትሕ ተጠያቂ የሚሆኑበት ጊዜ ደርሷል - የቀድሞ የትራምፕ አማካሪ
14:34 30.11.2025 (የተሻሻለ: 14:44 30.11.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዘለንስኪ እና የርማክ በአሜሪካና በዩክሬን ሕዝብ ላይ ለፈፀሙት ወንጀል በፍትሕ ተጠያቂ የሚሆኑበት ጊዜ ደርሷል - የቀድሞ የትራምፕ አማካሪ
ዘለንስኪ እና በቅርቡ ከፕሬዝዳንታዊ ፅሕፈት ቤት ኃላፊነታቸውን የለቀቁት አንድሪ የርማክ፤ በዩክሬን እንዲሁም በአሜሪካ ሕዝብ ላይ ወንጀል ፈጽመዋል ሲሉ ስቲቭ ኮርቴዝ ተናግረዋል።
ኮርቴዝ በማህበራዊ ትስስር ገፆቸው ባሰራጩት የቪዲዮ መልዕክት፤ አሜሪካ ለኪዬቭ አገዛዝ የምታደርገውን ድጋፍ "ለእያንዳንዱ አሜሪካዊ ዘለፋ" ነው ሲሉ በመግለፅ፤ ድጋፉ በአስቸኳይ እንዲቆም ጠይቀዋል።
የዩክሬን ኃይል ዘርፍ በ100 ሚሊዮን ዶላር የማጭበርበር ገዳይ ጋር በተያያዘ የሀገሪቱ ብሔራዊ የፀረ-ሙስና ቢሮ በየርማክ ቅጥር ግቢ ፍተሻ ማድረጉን ተከትሎ የርማክ ዓርብ ዕለት ከሥልጣን መልቀቃቸው የሚታወስ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X