በጊኒ-ቢሳው በወታደራዊ ኃላፊዎች የሚመራ አዲስ ጊዜያዊ መንግሥት ተቋቋመ
11:52 30.11.2025 (የተሻሻለ: 11:54 30.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በጊኒ-ቢሳው በወታደራዊ ኃላፊዎች የሚመራ አዲስ ጊዜያዊ መንግሥት ተቋቋመ
አዲሱ ሥራ አስፈፃሚ 23 ሚኒስትሮችን እና 5 ምክትል ሚኒስትሮችን ያቀፈ ሲሆን ሲቪል ግለሰቦችን እና ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችንም አካቷል።
ቁልፍ ሹመቶች የሚከተሉት ናቸው፦
ጆአዎ በርናርዶ ቪዬራ – የውጭ ጉዳይና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር፣
ብሪጋደዬር ጄኔራል ማማሳሊዩ ኢምባሎ – የሀገር ውስጥ ጉዳይና ሥርዓት ሕዝብ ሚኒስትር፣
ኡስና አንቶኒዮ ክዋዴ – የሚኒስትሮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት እና የፓርላማ ጉዳዮች ሚኒስትር፣
ካርሎስ ፒንቶ ፔሬይራ – የፍትሕና የሰብዓዊ መብቶች ሚኒስትር፣
ማማዱ ሙጄታባ ጃሎ – የኢኮኖሚ፣ የዕቅድ እና የክልል ውህደት ሚኒስትር፣
ሜጀር ጄኔራል ስቲቭ ላሳና ማንሳሊ – የብሔራዊ መከላከያ ሚኒስትር፣
ኮሞዶር ኩዪንሂን ናንቶቴ – የሕዝብ ጤና ሚኒስትር፣
ቨርጂኒያ ማሪያ ዳ ክሩዝ ጎዲንሆ ፒሬስ ኮሬያ – የዓሣ ሀብትና የባሕር ኢኮኖሚ ሚኒስትር፣
ጁኤልማ ኩባላ – የወጣቶች፣ የባሕል እና ስፖርት ሚኒስትር፣
ካዲ ፍሎረንስ ዳቦ ኮሬያ – የሴቶችና የማህበራዊ ትብብር ሚኒስትር።
የሽግግር ፕሬዝዳንቱ ጄኔራል ሆርታ ን'ታም አዲሱ መንግሥት “ሙስና እና የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውርን እንዲዋጋ” አሳስበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X