ኢራን የትራምፕን የቬንዙዌላ አየር ክልል መግለጫ “ለአቪዬሽን ደህንነት ታይቶ የማይታወቅ ስጋት” ስትል አወገዘች
10:56 30.11.2025 (የተሻሻለ: 11:04 30.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢራን የትራምፕን የቬንዙዌላ አየር ክልል መግለጫ “ለአቪዬሽን ደህንነት ታይቶ የማይታወቅ ስጋት” ስትል አወገዘች
የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጌኢ፤ ትራምፕ በቬንዙዌላ የአየር ክልል ዙሪያ በቅርቡ ያወጡት መግለጫ “የዘፈቀደ” እና “መሠረታዊ ዓለም አቀፍ ሕጎችንና ደንቦችን በግልፅ የጣሰ” ነው ማለታቸውን ጠቅሶ የመንግሥት የዜና ወኪል አይአርኤንኤ ዘግቧል።
ቃል አቀባዩ እርምጃው በቬንዙዌላ ሉዓላዊነት ላይ እየተወሰደ ያለ የ “ጠብ አጫሪና ሕገ-ወጥ ድርጊቶች” ሰፊ አካል ነው ብለውታል።
የእንደዚህ አይነት እርምጃዎች መቀጠል “ለሕግ የበላይነት፣ ለሰላምና ለዓለም አቀፍ ደህንነት አደገኛ መዘዞችን” ያስከትላል ሲሉም በማስጠንቀቅ፤ ቴህራን የትራምፕ አስተዳደር የሚከተለው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አቅጣጫ በጣም እንደሚያሳስባት ገልፀዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X