የአፍሪካ ደኖች ከሚስቡት የበለጠ ካርቦን እንደሚለቁ ጥናት አመላከተ
17:43 29.11.2025 (የተሻሻለ: 17:44 29.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ደኖች ከሚስቡት የበለጠ ካርቦን እንደሚለቁ ጥናት አመላከተ
ሳይንቲፊክ ሪፖርትስ በተሰኘው መጽሔት ላይ የታተመው አዲስ ጥናት፤ የአፍሪካ አህጉር ደኖች እ.ኤ.አ ከ2010 ወዲህ ካርቦን ከመሳብ ወደ ካርቦን ለቃቂነት (ምንጭ) መለወጣቸውን አሳይቷል።
ይህ አሳሳቢ ለውጥ የዓለማችን ሦስቱ ዋና ዋና የደን ክልሎች የአየር ንብረት ለውጥን ከማቃለል ይልቅ ለአየር ንብረት መዳከም አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉ ያመለክታል ሲል ጥናቱ ገልጿል።
የአፍሪካ ደኖች እ.ኤ.አ በ2010 እና በ2017 መካከል በየዓመቱ በግምት 106 ቢሊዮን ኪሎ ግራም ሥነ-ህይወት አጥተዋል። ኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ ማዳጋስካር እና ምዕራብ አፍሪካ ከፍተኛ መመናመን ደርሶባቸዋል።
ሳይንቲስቶቹ ለዚህ የጥፋት አዝማሚያ የግብርና መስፋፋት፣ የማዕድን ቁፋሮ እና የመሠረተ ልማት ዝርጋታ የመሰሉ የሰዎች እንቅስቃሴዎችን በዋና መንስዔነት ጠቅሰዋል።
የጥናቱ ዋና አዘጋጅ ፕሮፌሰር ሄይኮ ባልትዘር፤ እ.ኤ.አ በ2021 በግላስጎ የደን ምንጣሮን በ2030 ለማስቆም ቃል ቢገባም፤ "ለውጥ በበቂ ፍጥነት እየተመዘገበ አይደለም" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X