ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ለምዕራባውያን በማድላት የተመረጠ ፍትሕ ይተገብራል - ኬኒያዊ ፖለቲከኛ

ሰብስክራይብ

ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ለምዕራባውያን በማድላት የተመረጠ ፍትሕ ይተገብራል - ኬኒያዊ ፖለቲከኛ

"ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይሲሲ) ገለልተኛ አልነበረም፡፡ ሌሎች ሀገራትን እንዲቀጣ ወይም እንዳይቀጣ የሚያዘው ታላቅ ወንድም ያለው ይመስላል" ሲሉ የኬንያ ፕሬዝዳንታዊ እጩ ፕሮፌሰር ፍሬድሪክ ኦጎላ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

ፕሮፌሰር ኦጎላ በአይሲሲ መዋቅር ውስጥ ያለውን የጥቁሮች እና የነጮች አለመመጣጠንም አንስተዋል፡፡

"ወደ አይሲሲ ምክር ቤት እና ወደ ዓቃብያነ ሕግ ወንበር ስትሄድ በጣም ነጭ ነው። ነገር ግን ወደ ተከሳሾች ስትሄድ፤ በጣም ጥቁር ነው፡፡"

የኡዚማ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት፤ የኢኮኖሚ ጥገኝነት የአፍሪካ መሠረታዊ ተጋላጭነት መሆኑን የለዩ ሲሆን የምዕራባውያን የፋይናንስ ጥቅም አደጋ ላይ ሲወድቅ "ካፒታሊዝም ፍትሕ ላይ ይነግሳል" ሲሉ ሞግተዋል፡፡

"አፍሪካ ራሷን እስካላከበረች እና አፍሪካውያን እርስ በእርስ እስካልተዋደዱ ድረስ ልትከበር አትችልም" በማለት ውጫዊ ተቋማትን ከመደገፍ ይልቅ በዓለም አቀፍ የፍትሕ ጉዳዮች ላይ የተባበረ የአፍሪካ አቋም እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ፕሮፌሰር ኦጎላ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን መፍታት እንደሚያስፈልግ እና ፍትሕ ያለአድልዎ መተላለፍ እንዳለበት አጥብቀው ተናግረዋል፡፡

"አይሲሲ ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን ያለምንም አድልዎ እየተመለከተ ነውን? ተቋሙ ይህን ጥያቄ መመለስ አለበት፡፡"

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0