የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር የሕግ ዘርፍ ትብብሮችን አፀደቀ
15:32 29.11.2025 (የተሻሻለ: 15:54 29.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ከብሪክስ አባል ሀገራት ጋር የሕግ ዘርፍ ትብብሮችን አፀደቀ
በዛሬው ዕለት ባካሄደው 50ኛ መደበኛ ስብሰባ ከቻይና መንግሥት ጋር በደረሰው የወንጀል ጉዳዮች የጋራ የሕግ ትብብር ስምምነት ላይ ተወያይቶ አጽድቋል፡፡
በተጨማሪም ከቻይና እና ብራዚል መንግሥት ጋር የፍርደኞች ማስተላለፍ ስምምነትን በተመሳሳይ አጽድቋል፡፡
አስፈጻሚው አካል ከደቡብ አፍሪካ መንግሥት ጋር የተደረሰውን የአሳልፎ መስጠት ስምምነት እንዲሁ ተቀብሏል፡፡
ምክር ቤቱ ስምምነቶች ቢፀድቁ ኢትዮጵያ ከሀገራቱ ጋር ዉጤታማ የወንጀል መከላከል የሁለትዮሽ ትብብር የሕግ ማዕቀፍ ለመፍጠር ያስችላታል በማለት ረቂቅ አዋጆቹን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መርቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X