የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ መሪዎች በሚቀጥለው ሳምንት ትራምፕ ያሸማገሉትን የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ እንደሚፈራረሙ ተገለጸ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ መሪዎች በሚቀጥለው ሳምንት ትራምፕ ያሸማገሉትን የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ እንደሚፈራረሙ ተገለጸ
የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ መሪዎች በሚቀጥለው ሳምንት ትራምፕ ያሸማገሉትን የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ እንደሚፈራረሙ ተገለጸ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.11.2025
ሰብስክራይብ

የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ መሪዎች በሚቀጥለው ሳምንት ትራምፕ ያሸማገሉትን የሰላም ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ እንደሚፈራረሙ ተገለጸ

ለህዳር 25 የታቀደው ይህ ስብሰባ፤ አሜሪካ በጦርነት በምትታመሰው ምስራቅ ኮንጎ ያለውን ውጥረት ለመፍታት እንዲሁም በማዕድን በበለጸገው ክልል የምዕራባውያን የማዕድን ኢንቨስትመንቶችን ለመዘርጋት የምታደርገው ጥረት አካል ነው ሲል የምዕራባውያን ሚዲያ ዘገባ አመልክቷል።

የኮንጎ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ሺሰኬዲ ቃልአቀባይ የታቀደውን የስምምነት ፊርማ አረጋግጠዋል ተብሏል። የትራምፕ አስተዳደር በሰኔ ወር ያደራደረው ስምምነት ላይ የተመሠረተ ይሆናል።

የዲፕሎማሲ ጥረቱ የመጣው በሩዋንዳ ይደገፋል የሚባለው የኤም23 አማፂ ቡድን በዚህ ዓመት በሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች ሞት እና በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩት ደግሞ መፈናቀል ምክንያት የሆነውን ውጊያ ዳግም መቀጠሉን ተከትሎ ነው። ኪጋሊ በግጭቱ ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ የለኝም ስትል ማስተባበሏን ቀጥላለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0