ኢትዮጵያ በ2050 የአቪዬሽን የጋዝ ልቀትን ዜሮ ለማድረስ ማቀዷን ገለፀች
12:34 29.11.2025 (የተሻሻለ: 12:44 29.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በ2050 የአቪዬሽን የጋዝ ልቀትን ዜሮ ለማድረስ ማቀዷን ገለፀች
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ ሀገሪቱ የትራንስፖርት ዘርፉን ዘመናዊ ከማድረግ ባሻገር የካርቦን ዳይኦክሳይድ ልቀትንና የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ ጥረት እያደረገች እንደሆነ በዘላቂ የአቪዬሽን ነዳጅ የአዋጭነት ጥናት ውጤት ዙሪያ በተዘጋጀ መድረክ ላይ ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ የበካይ ጋዝ ልቀትን ለመቀልበስ ግንባር ቀደም ሚና እየተወጣች እንደምትገኝም በመድረኩ ተመላክቷል፡፡
ሀገሪቱ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በአካባቢ ጥበቃ እንዲሁም በአረንጓዴ አሻራ ተነሳሽነት ያከናወነቻቸው ተግባራቶች በአብነት ተነስተዋል፡፡
ዘላቂ አቪዬሽን ነዳጅ ከአቪዬሽን ኢንዱስትሪ 80 በመቶ የካርበን ልቀትን ለመቀነስ የሚያስችል የኃይል አማራጭ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X