የመንግሥት ሠራተኞች ከ2019 ጀምሮ የጤና መድን ተጠቃሚ ይሆናሉ ተባለ
20:13 28.11.2025 (የተሻሻለ: 20:24 28.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የመንግሥት ሠራተኞች ከ2019 ጀምሮ የጤና መድን ተጠቃሚ ይሆናሉ ተባለ
አገልግሎቱ በመጪው ዓመት ለማስጀመር በገንዘብ ሚኒስቴር 4.5 ቢሊዮን ብር መጽደቁን የኢትዮጵያ ጤና መድን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ተስፋዬ ወርቁ አስታውቀዋል፡፡
በዘንድሮው ዓመት በጤናው ዘርፍ የተሰማሩ ከ500 ሺህ በላይ ሠራተኞች ለአገልግሎቱ መመዝገባቸውን ተናግረዋል፡፡
“መደበኛ በሆኑ የሥራ መስኮች የተሰማሩ ዜጎች የጤና መድን አገልግሎት እንዲያገኙ ታስቦ የተዘጋጀው የማኅበራዊ ጤና መድን አገልግሎት በአዋጅና ደንብ ከጸደቀ 14 ዓመታትን ቢያስቆጥርም ሳይተገበር ቆይቷል፤ ዘንድሮ ግን የተሻለ ተስፋ አለ” ሲሉ ገልፀዋል፡፡
አዋጁ ከሠራተኛው ደመወዝ ሦስት በመቶው እንዲቆረጥና የፌዴራልና የክልል መንግሥታትም ለተቀጣሪዎቻቸው ይህን እንዲሸፍኑ ይደነግጋል።
ዋና ዳይሬክተር በቀጣዩ ዓመት ሁሉም የመንግሥት ሠራተኛ የጤና መድን ተጠቃሚ እንዲሆን የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት በጀት ይይዛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ መናገራቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X