ታንዛኒያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን አንዳንድ ስምምነቶች ለመተው ጊዜው አሁን ነው - ቤኒናዊ የፖለቲካ ተንታኝ
13:13 28.11.2025 (የተሻሻለ: 13:14 28.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ታንዛኒያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን አንዳንድ ስምምነቶች ለመተው ጊዜው አሁን ነው - ቤኒናዊ የፖለቲካ ተንታኝ
የአውሮፓ ሕብረት ፓርላማ በታንዛኒያ ድኀረ ምርጫ ቀውስ ላይ የውሳኔ ሐሳብ እንደማሰናዳቱ ወደ ጤናማ ትብብሮች ለመሸጋገር ጊዜው አሁን ነው ሲሉ ሞዴስት ዶሱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
የታንዛኒያ የኢንተርኔት ፖሊሲ የአፍሪካን ሀብቶች ለማግኘት በሚፈልጉ ምዕራባውያን አገሮች ተጽዕኖ ሊደረግበት ይችላል ሲሉ እምነታቸውን አጋርተዋል።
"እነዚህን ሀብቶች ይፈልጋሉ፣ ነገር ግን አሁን ያሉት ባለሥልጣናት እንዲኖራቸው እየፈቀዱ ስላልሆነ፣ ባለሥልጣናቱን ሕጋዊነት ለማሳጣት መንገድ ይፈልጋሉ" ሲሉ ዶሱ ተናግረዋል።
እንደ ፈረንሳይ፣ እንግሊዝ እና ቤልጂየም ያሉ አገራት በታንዛኒያ የተቃውሞ ሰልፎችን ሊደግፉ ይችላሉ ብለዋል። ዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤትም በታንዛኒያ ጉዳዮች ውስጥ ጣልቃ ሊገባ እንደሚችልም አክለዋል።
"ይህ ፍርድ ቤት ፍትሐዊ አለመሆኑ ግልጽ ነው። ድርብ መስፈርት ይጠቀማል። የራሱን ራዕይ የማይጋሩ ደካማ ሀገራት መሪዎችን ብቻ ይዳኛል" ሲሉ ገልጸዋል።
ህዳር 16 ቀን ታንዛኒያ የአውሮፓ ሕብረት ፓርላማ በታንዛኒያ ውስጥ ክስ ስለቀረበባቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ውይይት ለማካሄድ ማቀዱን ተከትሎ በፖለቲካዊ ጣልቃገብነት ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X