- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

ከስደት ወደ ተጽዕኖ ፈጣሪነት፡ የአፍሪካ ዲያስፖራዎች ለአፍሪካ ሉዓላዊነት

ከስደት ወደ ተጽዕኖ ፈጣሪነት፡ የአፍሪካ ዲያስፖራዎች ለአፍሪካ ሉዓላዊነት
ሰብስክራይብ

በቅኝ ግዛት ዘመን አፍሪካ ነፃ እንድትወጣ የአፍሪካ ዲያስፖራዎች ትልቅ ሚና ተጫውተዋል — የአፍሪካ ሀገራት እርስ በርስ መተሳሰርና ውስጣቸውን ማጠናከር አለባቸው '' ሲሉ በወለጋ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ምሁሩ ጉተማ ዳንኤል (ዶ/ር ) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ሶቨርኒቲ ሶርስስ በዛሬው መርሃ ግብሩ በክፍል አንድ የአፍሪካ ዲያስፖራዎች በመላው ዓለም ቁልፍ ሚና በተመለከተ በወለጋ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ምሁሩ ጉተማ ዳንኤል (ዶ/ር) አነጋግሯቸዋል።

ከምዕራባዊያን እርዳታ ተላቅቆ የውስጥ አቅምን ለማጎልበትና ከድህነት ለመውጣት የሚደረግ ትግልን በተመለከተ በክፍል ሁለት ከፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች መምህሩ ሀዋቂ በቀለ ጋር የተደረገው ቆይታም ሌላኛው ጉዳያችን ነው።

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡-
አዳዲስ ዜናዎች
0