ግብፅ የሱዳን ወደቦችን ዘመናዊ በማድረግ ሂደት ውስጥ እንደምትሳተፍ አስታወቀች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱግብፅ የሱዳን ወደቦችን ዘመናዊ በማድረግ ሂደት ውስጥ እንደምትሳተፍ አስታወቀች
ግብፅ የሱዳን ወደቦችን ዘመናዊ በማድረግ ሂደት ውስጥ እንደምትሳተፍ አስታወቀች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.11.2025
ሰብስክራይብ

ግብፅ የሱዳን ወደቦችን ዘመናዊ በማድረግ ሂደት ውስጥ እንደምትሳተፍ አስታወቀች

የግብፅ ልዩ ልዑካን ቡድን በታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ ሱዳንን እንደሚጎበኙ የስዊዝ ቦይ (ካናል) ባለሥልጣን ዳይሬክተር ኦሳማ ራቢያ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

"ከስዊዝ ካናል ባለሥልጣን የተውጣጣ የሥራ ቡድን የመሠረተ ልማት ግንባታን ለማዘመን እና ሰራተኞችን ለማሰልጠን እቅድ ለማዘጋጀት የሱዳን ወደቦችን ይጎበኛል" ብለዋል።

ከሱዳን የወደብ ባለሥልጣን ዳይሬክተር ከሆኑት ከጂላኒ መሐመድ ጂላኒ ጋር ውይይቶች በመካሄድ ላይ ናቸው ሲሉም ጠቁመዋል።

የሱዳን ወደቦች የተፈጥሮ ሀብቶችን ለመላክ እና የባሕር በር ለሌላቸው ጎረቤት አገራት ኢኮኖሚ ወሳኝ የንግድ መግቢያዎች ሆነው ያገለግላሉ። ሆኖም አሁን ያለውን ግጭት ተከትሎ የንግድ ልውውጥ በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0