የአገሪቱን የዓለም አቀፍ ገበያ ድርሻን ያሳድጋል የተባለለት የኢትዮጵያ ስፔሻሊቲ ቡና ማኅበር ተመሠረተ
20:31 26.11.2025 (የተሻሻለ: 20:34 26.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአገሪቱን የዓለም አቀፍ ገበያ ድርሻን ያሳድጋል የተባለለት የኢትዮጵያ ስፔሻሊቲ ቡና ማኅበር ተመሠረተ
አርሶ አደሮችን፣ ምርት ላኪዎችን፣ ሕብረት ሥራ ማኅበራትን፣ ተመራማሪዎችን እና የመንግሥት ተቋማትን ባንድ ያሰባሰበው ማኅበሩ ወደ ውጭ የሚላኩ የፕሪሚየም ቡና ምርቶች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡
︎የአገሪቱን ምርጥ የቡና ዓይነቶች ለይቶ በማውጣትና በማስተዋወቅ ላይ የሚያተኩረውን "ምርጥ የኢትዮጵያ ቡና" የተሰኘ አገር አቀፍ ተነሳሽነት ከግብ ማድረስ ዋነኛ ተልዕኮው እንደሚሆን የአገር ውስጥ የግል ሚዲያ ዘግቧል።
የማኅበሩ ቁልፍ ተግባራት፦
የጥራት ማረጋገጫ፣
ክትትል ማድረግ፣
ጥናት እና ምርምር፣
ለአርሶ አደሮች የክህሎት ማበልጸጊያ ሥልጠና መስጠት እና
የአገር ውስጥ አምራቾችን ከዓለም አቀፍ ገበያዎች ጋር ማገናኘት ናቸው፡፡
በሰስ ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X