የሩሲያ የዓሣ አምራች ኩባንያዎች በአፍሪካ በትብብር የመሥራት ፍላጎት አላቸው - የክሬምሊን ቃል አቀባይ
19:09 26.11.2025 (የተሻሻለ: 19:14 26.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ የዓሣ አምራች ኩባንያዎች በአፍሪካ በትብብር የመሥራት ፍላጎት አላቸው - የክሬምሊን ቃል አቀባይ
የሩሲያ የዓሣ አስጋሪ ኩባንያዎች በአፍሪካ አኅጉር በሚኖራቸው ትብብር ላይ ኢንቨስት እያደረጉ እንደሆነ እና ማድረጋቸውንም እንደሚቀጥሉ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
የቃል አቀባዩ አስተያየት የሩሲያን ታላቅ የአፍሪካ ጉዞ በተመለከተ በወጣው ዘገባ ውስጥ ተካቷል፡፡ የሩስያ ይህ ጉዞ ሦስት የሩሲያ መርከቦችን ማለትም አትላንቲስ እና አትላንትኒሮ የተባሉ የምርምር መርከቦችን እንዲሁም ክሩዘንሽተርን የተባለውን ማሠልጠኛ መርከብ ያካትታል።
የ2024-2025 ታላቁ ጉዞ ከካሊኒንግራድ ነሐሴ 15 ተጀምሯል። ይህ ጉዞ በምዕራብ አፍሪካ አገራት እና በምዕራብ ሕንድ ውቅያኖስ ብቸኛ የኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ ሁለት ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ያካትታል።
የዚህ ሳይንሳዊ የምርምር ተልዕኮ ዓላማ በእነዚህ አካባቢዎች የውሃ ውስጥ ሥነ ሕይወታዊ ሀብቶችን ማሰስ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X