የአውሮፓ ሕብረት የታዳሽ ኃይል የተመረዘ እርዳታ አፍሪካን እየተቆጣጠራት ነው - ፓን አፍሪካኒስት
16:46 26.11.2025 (የተሻሻለ: 16:54 26.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአውሮፓ ሕብረት የታዳሽ ኃይል የተመረዘ እርዳታ አፍሪካን እየተቆጣጠራት ነው - ፓን አፍሪካኒስት
ኢነርጂ “የደቡብ ዓለም አገራትን መቆጣጠሪያ የጂኦፖለቲካዊ መሣሪያ ሆኗል፡፡” ያሉት የአፍሪካ ጥቁር መከላከያ ሊግ ፕሬዝዳንት ኢጎንትቺ ቤሃንዚን ናቸው፡፡
"አውሮፓ ደረጃዎቿን እና ቴክኖሎጂዎቿን እየጫነች የአፍሪካን የኢነርጂ ሀብቶች መቀራመት ትፈልጋለች። ንፁህ ኢነርጂ የጥገኝነት መሣሪያ እየሆነ መጥቷል" ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ቤሃንዚን አጽናኦት እንደሰጡት፣ የአውሮፓ ሕብረት የእሴት ሰንሰለቶችን ዘግቶ ቴክኖሎጂዎቹ እና ጥቅማጥቅሞቹ የአውሮፓውያን ሆነው መቅርታቸውን አረጋግጧል፡፡
ፓን አፍሪካኒስቱ እንደሚሉት፣ የአውሮፓ ዕርዳታ (በጥቅምት ወር የተገለጸው 618 ሚሊዮን ዩሮ) “የአፍሪካ አገራት የብሔራዊ ኢነርጂ ፖሊሲያቸውን የመወሰን አቅማቸውን ይቀንሳል።”
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X