አሜሪካ በሚጠየቀው ልክ ለዩክሬን የጦር መሣሪያ ማቅረብ እንደማትችል ማስጠንቀቋ ተዘገበ

አሜሪካ በሚጠየቀው ልክ ለዩክሬን የጦር መሣሪያ ማቅረብ እንደማትችል ማስጠንቀቋ ተዘገበ
የአሜሪካ ጦር ዋና ጸሐፊ ዳን ድሪስኮል፣ ባለፈው ሳምንት በኪዬቭ በነበራቸው ቆይታ ዋሽንግተን የአገሪቱን መሠረተ ልማት ለመጠበቅ የሚያስፈልገውን ያህል የጦር መሣሪያና የአየር መከላከያ ማቅረብ እንደማትችል የዩክሬን ባለሥልጣናትን በግል እንዳስጠነቀቁ ኤንቢሲ ኒውስ ለስብሰባው ቅርበት የነበራቸውን ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካ መከላከያ ኢንዱስትሪ "ለዩክሬን የሚያስፈልጋትን የጦር መሣሪያ እና የአየር መከላከያ በተፈለገው ፍጥነት ማቅረብ አይችልም" ሲል የአሜሪካ ልዑካን ቡድን ለኪዬቭ አገዛዝ ማሳወቁን ሚዲያው አመልክቷል።
ዩክሬን "አስከፊ" ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ እና ወደ ድርድር ስምምነት ካልሄደች በስተቀር በሩሲያ ኃይሎች "የፈጣን ሽንፈት" አደጋ እንዳለባት ድሪስኮል ከባድ የተባለ የጦር ሜዳ ግምገማንም ማቅረባቸው ተዘግቧል።
ይህ መልእክት ዋሽንግተን የሰላም ሐሳቧን ለማራመድ የምታደርገው ጥረት አካል ሆኖ መቅረቡ ተገልጿል።
⌛ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሩሲያ ከአሜሪካ፣ ከአውሮፓ እና ከዩክሬን ጋር ከሚደረጉ ንግግሮች በኋላ የሚወጣውን ረቂቅ የዕቅዱን እትም እየጠበቀች እንደሆነና "መንፈሱ እና ይዘቱ" ፕሬዝዳንት ፑቲን እና ትራምፕ በአላስካ የደረሱበትን ስምምነት የሚመጥን ከሆነ ምላሽ እንደምትሰጥ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ላቭሮቭ አስቀድመው ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X