ጋምቢያ ለካሜሮን የተቃዋሚ መሪ ኢሳ ችሮማ ባካሪ የሰብዓዊ ጥገኝነት መስጠቷን አረጋገጠች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱጋምቢያ ለካሜሮን የተቃዋሚ መሪ ኢሳ ችሮማ ባካሪ የሰብዓዊ ጥገኝነት መስጠቷን አረጋገጠች
ጋምቢያ ለካሜሮን የተቃዋሚ መሪ ኢሳ ችሮማ ባካሪ የሰብዓዊ ጥገኝነት መስጠቷን አረጋገጠች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.11.2025
ሰብስክራይብ

ጋምቢያ ለካሜሮን የተቃዋሚ መሪ ኢሳ ችሮማ ባካሪ የሰብዓዊ ጥገኝነት መስጠቷን አረጋገጠች

ችሮማ "በሰብዓዊ ምክንያቶች ብቻ" ጥቅምት 28 ቀን ጋምቢያ እንደደረሱ ባንጁል በትናንትናው ዕለት ባወጣችው ይፋዊ መግለጫ ገልፃለች።

ጊዜያዊ ጥገኝነቱ የካሜሩንን የድህረ-ምርጫ ውጥረት ተከትሎ የተሰጠ ነው። መግለጫው እርምጃው "የካሜሩን ናሽናል ሳልቬሽን ፍሮንት" ፓርቲ ፕሬዝዳንትን ደህንነት ለማረጋገጥ ያለመ እንደሆነ አስታውቋል።

ጋምቢያ አክላም በግዛቷ ላይ የሚፈፀሙ አፍራሽ ተግባሮችን እንደማትታገስ አስገንዝባለች።

ባንጁል በካሜሩን ያለውን ቀውስ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ናይጄሪያን ጨምሮ ከክልላዊ አጋሮች ጋር እየሠራች እንደሆነና ለምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ ሰላም እና መረጋጋት ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።

የካሜሮን መንግሥት እስካሁን ምንም ዓይነት ይፋዊ ምላሽ አልሰጠም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0