‘በዶላር የሚከፈል ዕዳ ያለፈ ታሪክ መሆን አለበት’ - የደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚስት
19:55 23.11.2025 (የተሻሻለ: 20:04 23.11.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
‘በዶላር የሚከፈል ዕዳ ያለፈ ታሪክ መሆን አለበት’ - የደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚስት
ደቡብ አፍሪካ በቡድን 20 ጉባኤ የያዘችው አቋም ሰፊ የጂኦፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥን የሚያመለክት እና ይህ ለውጥ ቢዘገይም በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ዶ/ር ንታቢሰንግ ሞሌኮ ተናግረዋል።
ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት አሰተያየት፤ ከዋሽንግተን ጋር ያለው ግንኙነት ከተበላሸ ደቡብ አፍሪካ የንግድ አድማሷን እንደምታሰፋ ገልጸዋል። ትርጉም ያለው ንግድ ለመፍጠር አዳዲስ ስምምነቶችን እና የጉምሩክ መሰናክሎችን መፍታት እንዳለ ሆኖ፤ ሀገሪቱ የንግድ እንቅስቃሴዎቿን ወደ ብሪክስ አጋሮቿ ታዞራለች ሲሉ አብራርተዋል።
ሞሌኮ፤ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ አስተዳደርን በተመለከተ፤ በአየር ንብረት ፋይናንስ እና የዕዳ እፎይታ ዙሪያ ፍትሐዊ ስምምነት እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ሰጥተዋል።
🟢 በታሪክ ጎጂ ጋዞችን የለቀቁ ሀገራት የሽግግሩን ሂደት መሸከም እንዳለባቸው ሞግተዋል። በተመሳሳይ አፍሪካ ከአህጉራዊው ነጻ የንግድ ቀጣና ሙሉ በሙሉ እንድትጠቅም የሚያስፈልጋትን መሠረተ ልማት እና አቅም መገንባት አለባት ብለዋል።
ባለሙያዋ የአፍሪካ ዓለም አቀፍ ውክልና እየጠነከረ መምጣቱንም ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X