የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሀገር ውስጥ የመማሪያ መጻሕፍት ማተሚያ ድርጅት በሽርክና ሊያቋቁም ነው
18:07 23.11.2025 (የተሻሻለ: 18:14 23.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሀገር ውስጥ የመማሪያ መጻሕፍት ማተሚያ ድርጅት በሽርክና ሊያቋቁም ነው
የሀገሪቱን ሀብቶች እና የሀብት ምንጮች የሚያስተዳድረው ግዙፍ ተቋም፤ ከጃፓኑ ቶፓን ግራቪቲ ጋር ሽርክና በመፍጠር የመማሪያ መጻሕፍት ማተሚያ ኩባንያ ሊቋቋም እንደሆነ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ከኩባንያው ጋር ያደረገውን ውይይትና ስምምነት በመጪዎቹ ጥቂት ቀናት ለቦርድ አቅርቦ እንደሚያጸድቅ ተዘግቧል።
በሽርክና በሚቋቋመው ማተሚያ ድርጅት 49 በመቶው ድርሻ የሆልዲንጉ ሲሆን ቶፓን ግራቪቲ የ51በመቶ ድርሻ እንደሚይዝ ተመላክቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X