ግብፅ በጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ የጋዛ ሰላም እንዲፀና ግፊት አደረገች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱግብፅ በጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ የጋዛ ሰላም እንዲፀና ግፊት አደረገች
ግብፅ በጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ የጋዛ ሰላም እንዲፀና ግፊት አደረገች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.11.2025
ሰብስክራይብ

ግብፅ በጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ የጋዛ ሰላም እንዲፀና ግፊት አደረገች

በጉባኤው ላይ ንግግር ያደረጉት የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ፤ የትራምፕ አስተዳደር የጋዛ ዕቅድ ሁለተኛ ምዕራፍ በፍጥነት ሥራ ላይ ሊውል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የተኩስ አቁም እና የሰብዓዊ ልውውጦችን ያካተተው እና በፍጥነት ሁኔታውን ለማረጋጋት እና ለውይይት መሠረት ለመጣል ያለመው የመጀመሪያው ምዕራፍ በአንፃራዊነት ስኬታማ ሆኖ ታይቷል።

ለበርካታ ዓመታት ታስቦ የተዘጋጀው ሁለተኛው ምዕራፍ ጋዛን ከወታደራዊ ኃይል ነፃ ማድረግ እና መልሶ ግንባታን ያካትታል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

ግብፅ በጋዛ አፋጣኝ መልሶ ግንባታ ዙሪያ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ለማዘጋጀት ዝግጁ ነች።

የቡድን 20 አባል ሀገራት በንቃት እንዲሳተፉ ይፋዊ ጥሪ ቀርቧል።

የሻርም ኤል-ሼክ የሰላም ጉባኤ "ይበልጥ የተረጋጋ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ብልፅግና የሰፈነበት" መካከለኛው ምስራቅ ለመፍጠር መንገድ ሊጠርግ ይገባል።

የቡድን 20 መሪዎች በመጨረሻ መግለጫቸው በፍልስጤም፣ በሱዳን፣ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዩክሬን "ፍትሐዊ፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ" ሰላም ለማምጣት ቁርጠኛ እንደሆኑ ገልፀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0