"አድማ ጥሩ ውጤት የሚያስገኝ አካሄድ አይደለም" - ደቡብ አፍሪካ ለቡድን 20 አንድነት እና ኢንቨስትመንት ጥሪ አቀረበች
19:59 22.11.2025 (የተሻሻለ: 20:04 22.11.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
"አድማ ጥሩ ውጤት የሚያስገኝ አካሄድ አይደለም" - ደቡብ አፍሪካ ለቡድን 20 አንድነት እና ኢንቨስትመንት ጥሪ አቀረበች
የደቡብ አፍሪካ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዴቪድ ማሶንዶ፤ ዓለም አቀፍ ውጥረት በተንሰራፋበት በዚህ ወቅት የትብብር አስፈላጊነት ላይ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ማሶንዶ፤ የደቡብ አፍሪካ የቡድን 20 ሊቀመንበርነት ደቡባዊው ዓለም በተለይም አፍሪካ የዓለምን ኢኮኖሚ ስርዓት እንደገና እንዲቀርፁ ወሳኝ ወቅት እንደሆነ ከስፑትኒክ ጋር ባደረጉት ቆይታ አብራርተዋል።
ከወጣት አምራች ኃይል የሕዝብ ብዛት እና "ለካርቦን ቅነሳ ወሳኝ የሆኑ ማዕድናት" ጋር ተዳምሮ፤ አፍሪካ ጥሬ እቃዎችን ወደ ውጭ ከመላክ ባለፈ "እሴት በመጨመር፤ የአኅጉሪቱን ኢንዱስትሪ ለማሸጋገር" መንቀሳቀስ እንዳለባት አስገንዝበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X