ደቡብ አፍሪካ የአሜሪካን ግፊት በመቋቋም በቡድን 20 ጠንካራ፣ አፍሪካ-ተኮር የመሪዎች መግለጫ አወጣች
ደቡብ አፍሪካ የአሜሪካን ግፊት በመቋቋም በቡድን 20 ጠንካራ፣ አፍሪካ-ተኮር የመሪዎች መግለጫ አወጣች
በአፍሪካ ምድር ላይ በተካሄደው የመጀመሪያው የቡድን 20 ስብሰባ ዛሬ በጆሃንስበርግ የጸደቀው ሰነድ ጠንካራ እና ባለብዙ-ዋልታ ድምጽ የተንፀባረቀበት ነው።
ከመግለጫው የተገኙ ዋና ዋና ነጥቦች፡-
🟠 ለአለም አቀፍ ሕግ እና ሉዓላዊነት የጸና ቁርጠኝነት፦ መሪዎች በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተርን እንደሚመሩ በማረጋገጥ በሲቪሎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን አውግዘዋል። እንዲሁም በሱዳን፣ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ፣ በፍልስጤም እና የዩክሬንን ጨምሮ ለዓለም አቀፍ ግጭቶች የሰላማዊ መፍትሄ ጥሪ አቅርበዋል።
🟠 አፍሪካ የዓለም አቀፍ አስተዳደር ማዕከል፦ መግለጫው በዓለም አቀፍ ውሳኔ አሰጣጥ ላይ የአፍሪካን ድምፅ አጉልቷል። በተጨማሪም የአፍሪካ ሀገራት የንግድ እና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችን በማሻሻል ኢንቨስትመንት እንዲስቡ የሚረዳ የቡድን 20 ትብብር አካል የሆነውን ኮምፓክት ዊዝ አፍሪካ እና የአፍሪካ ተሳትፎ ማዕቀፍ ያሉ ዋና ዋና ተነሳሽነቶችን አፅድቋል።
🟠 የኃይል ተደራሽነትን እና ፍትሐዊ ሽግግሮችን ማፋጠን፦ ቡድን 20 ታዳሽ የኃይል አቅምን በሶስት እጥፍ ለማሳደግ፣ ንጹህ የማብሰያ ዘዴዎችን ተደራሽነት ለማስፋት እና በ2030 300 ሚሊዮን ሰዎችን ከኤሌክትሪክ ጋር ለማገናኘት ያለመውን ሚሽን 300 የመሳሰሉ አፍሪካ-ተኮር ተነሳሽነቶችን ደግፏል።
🟠 ወሳኝ ማዕድናትን ለልማት ማዋል፦ አዲሱ የወሳኝ ማዕድናት ማዕቀፍ ማዕድናት ከሚገኙበት ስፍራ እሴት መጨመር እና በማዕድን የበለጸጉ ሀገራት ሉዓላዊ መብቶች እንዲጠበቁ ይደግፋል።
🟠 የዕዳ ቅነሳ እና የፋይናንስ ማሻሻያ፦ መሪዎች ጠንካራ የዕዳ ዘላቂነት ስልቶችን፣ በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) አስተዳደር ውስጥ ለታዳጊ ሀገራት የላቀ ውክልና ጥሪ አቅርበዋል።
🟠 የምግብ ዋስትና እና የኡቡንቱ መርሆዎች፦ “የኡቡንቱ መንገድ” የምግብ ዋጋ መዋዠቅን ለመቀነስ እና አካታች አፍሪካ-መር የግብርና መቋቋም አቅምን ለማራመድ ኢላማው አድርጓል።
🟠 የሰው ሠራሽ አስተውህሎት (ኤአይ) ለአፍሪካ፦ መግለጫው የኮምፒውተር ተደራሽነትን፣ የክህሎት ልማትን እና አፍሪካ-ተኮር የኤአይ አቅሞችን ለማሳደግ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ለአፍሪካ ተነሳሽነትን ይፋ አድርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X