'ታሪካችን የፀጥታ አብዮት ነው'፤ የዕድገት ጽንሰ ሃሳብን ዳግም ልንመለከት ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ሰብስክራይብ

'ታሪካችን የፀጥታ አብዮት ነው'፤ የዕድገት ጽንሰ ሃሳብን ዳግም ልንመለከት ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቡድን 20 የመሪዎች ስብሰባ ትሕትና፣ ተስፋ እና ቆራጥ ለውጥ ላይ የተመረኮዘ መልዕክት ያስተላለፉበትን ንግግር አድርገዋል።

የራዕያቸው ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦

እየተካሄደ ያለ ጉዞ፦ ኢትዮጵያ በጥንታዊ ሥልጣኔ እና ጥንካሬ ላይ በመመሥረት መጪ ጊዜዋን የአንድነት፣ የትብብር እና የጋራ ዕድገት አስተሳሰብ ማዕከል በሆነው የመደመር ፍልስፍና እየቀረጸች ነው።

በሂደት ያለው የፀጥታ አቢዮት፦ “ታሪካችን በቆራጥ እርምጃዎች የተሞላ፣ የሚቻለውን ዳግም በፀጥታ እየፃፈ ያለ አቢዮት ነው” ብለዋል። ከተሞች እየፈጠሩ ነው፣ እርሻዎች እየዘመኑ ነው እና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች እድሎችን ዳግም እየወሰኑ ነው።

አካታችነት ለቅልጥፍና፦ ዐቢይ እያንዳንዱን አርሶ አደር፣ አዳዲስ ሀሳብ አመንጪ እና ሥራ ፈጣሪን ማብቃት አጠቃላይ ኢኮኖሚውን እንደሚያጠናክር አፅንዖት ሰጥተዋል።

ችግሮችን ወደ ለውጥ መቀየር፦  ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል፣ ዲጂታል መሠረተ ልማት እና የአየር ንብረት ተስማሚ ግብርና በመጠቀም ከድርቅ እስከ ግጭት ላሉ ጉዳዮች ምላሽ እየሰጠች ነው።

ኢትዮጵያ ቡድን 20 እንዲቀበላቸው የምትገፋባቸው ሦስት ዓለም አቀፍ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች፦

ዕዳ፦ "የተማሩ ልጆች፣ ዘመናዊ ሆስፒታሎች እና ጠንካራ መሠረተ ልማት" እንዲኖር በማድረግ የዕዳ ስረዛ እውነተኛ ኢንቨስትመንት መሆኑን ማረጋገጥ፣

የአየር ንብረት፦ 48 ቢሊዮን ችግኞችን የተከለችው ኢትዮጵያ፤ በዕዳ-አየር ንብረት ልውውጥ እና በአረንጓዴ እሴት ሰንሰለቶች የአካባቢ ጥበቃ እንዲሰፋ ጥሪ ታቀርባለች፣

ኃይል እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፦ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስከ 2030 ሀገር አቀፍ የዲጂታል መሠረተ ልማት በመዘርጋት፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የተሳሰረ፣ ታዳሽ እና ከካርበን ነፃ የሆነ የወደፊት ጊዜን ትመኛለች።

ዐቢይ በጠንካራ ንግግር ሀሳባቸውን ሰደመድሙ፦

“በሀገር ውስጥ ምርትን ብቻ ሳይሆን የማኅበረሰቡን የመቋቋም እና የመላመድ አቅምን እንቁጠር፤ ምክንያቱም ይህ ነው በመጨረሻ ልማትን ዘላቂ የሚያደርገው። ኢትዮጵያ በመደመር ፍልስፍና ላይ ተመስርታ ለዚህ የጋራ ዓለም አቀፍ ጉዞ አስተዋፅዖ ለማድረግ ዝግጁ ናት።”

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0