ባለብዝሃ ወገን መድረክ፣ የአፍሪካ ቀዳሚ አጀንዳዎች እና ለአካታች ዓለም አቀፍ ትብብር ጥሪ፤ የራማፎሳ የቡድን 20 የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ንግግር ትኩረቶች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱባለብዝሃ ወገን መድረክ፣ የአፍሪካ ቀዳሚ አጀንዳዎች እና ለአካታች ዓለም አቀፍ ትብብር ጥሪ፤ የራማፎሳ የቡድን 20 የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ንግግር ትኩረቶች
ባለብዝሃ ወገን መድረክ፣ የአፍሪካ ቀዳሚ አጀንዳዎች እና ለአካታች ዓለም አቀፍ ትብብር ጥሪ፤ የራማፎሳ የቡድን 20 የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ንግግር ትኩረቶች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.11.2025
ሰብስክራይብ

ባለብዝሃ ወገን መድረክ፣ የአፍሪካ ቀዳሚ አጀንዳዎች እና ለአካታች ዓለም አቀፍ ትብብር ጥሪ፤ የራማፎሳ የቡድን 20 የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ንግግር ትኩረቶች

በጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ መክፈቻ ሲሪል ራማፎሳ ያደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮች፦

ደቡብ አፍሪካ የቡድን 20 አመራርነቷን በጥንቃቄ እና በትጋት ለመወጣት ባለፈው ዓመት በደቡብ አፍሪካ፣ በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ 130 የሚጠጉ ስብሰባዎችን መርታለች።

የቡድን 20 አጀንዳ ከማክሮ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አልፎ ንግድ፣ ዘላቂ ልማት፣ ጤና፣ ትምህርት፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ግብርና፣ ኢነርጂ፣ አካባቢን እና የአየር ንብረት ለውጥን ያካተተ ሆኗል።

ደቡብ አፍሪካ የቡድን 20 መስራች አባል እንደመሆኗ መጠን የደቡባዊ ዓለም እና የአፍሪካ የልማት ቅድሚያዎች በቡድን 20 አጀንዳ ላይ በጥንካሬ እና በቋሚነት እንዲቀመጡ አድርጋለች።

የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ መግለጫ መጽደቅ ለዓለም፤ “ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሊሠራ እንደሚችልና እንደሚሠራ” መልዕክት ያስተላልፋል።

መግለጫው “ማንም ሰው፣ ማህበረሰብ ወይም ሀገር ወደኋላ አይቀርም” የሚለውን የቡድን 20 መሪዎች ቃል በማረጋገጥ የተስፋ እና የአብሮነት መልዕክት ያስተላልፋል።

ቡድን 20 ዓለም አቀፍ ችግሮች በትብብር፣ በመተባበር እና በአጋርነት ብቻ ሊፈቱ እንደሚችሉ በመገንዘብ የዓለም አቀፍ ግንኙነትን አስፈላጊነት ያጎላል።

ዓለም አቀፉን የፋይናንስ ሥርዓት የማሻሻል ሥራ ተቋማትን ማጠናከር፣ አካታችነትን ማሳደግ እና አሁን ላሉና ለወደፊቱ ፈተናዎች ማዘጋጀትን መቀጠል አለበት።

በአፍሪካ የተካሄደ የመጀመሪያው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ እንደመሆኑ መጠን የአፍሪካ አህጉርንና የዓለምን ተስፋዎች እና ምኞቶች ማንፀባረቅ እንዲሁም የመጀመሪያውን የአፍሪካ የቡድን 20 ፕሬዝዳንትነት ዋጋ፣ ክብር እና ተፅዕኖ መጠበቅና ማሳደግ አለበት።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0