በአፍሪካ የመጀመሪያውን የቡድን 20 ፕሬዝዳንትነት ዋጋ፣ ከፍታ እና ተጽዕኖ የሚያሳንስ ማንኛውንም ነገር መፍቀድ የለብንም - ራማፎሳ

ሰብስክራይብ

በአፍሪካ የመጀመሪያውን የቡድን 20 ፕሬዝዳንትነት ዋጋ፣ ከፍታ እና ተጽዕኖ የሚያሳንስ ማንኛውንም ነገር መፍቀድ የለብንም - ራማፎሳ

"ይህ በአፍሪካ የሚካሄድ የመጀመሪያው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ በመሆኑ የዚህን አህጉር እና የዓለም ሕዝቦች ተስፋዎች መሸከምና ማንፀባረቅ አለበት" ሲሉ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በጆሃንስበርግ በተካሄደው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባኤ መክፈቻ ላይ ተናግረዋል፡፡

ራማፎሳ የጉባኤው ኃላፊነት የቡድን 20ን ተዓማኒነት ከማዳከም ይልቅ ማጠናከር እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።

ዋሽንግተን በይፋዊ መድረኩ ላይ እንደማትገኝ ማረጋገጧን ተከትሎ የመክፈቻው ስብሰባ ያለ አሜሪካ ተሳትፎ ቀጥሏል። አድማው ዶናልድ ትራምፕ የደቡብ አፍሪካን አዘጋጅነት ከተቹ እና ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን በደል ይደርስባቸዋል ብለው ከወነጀሉ በኋላ የመጣ ነው።

ፕሪቶሪያ አሜሪካ ባትሳተፍም ጉባኤው በውጤታማነት እንደሚካሄድ የገለፀች ሲሆን ሀገሪቱ በህዳር 2025 መጨረሻ ፕሬዝዳንትነቱን ለዩናይትድ ስቴትስ ታስተላልፋለች።

የፕሬዝዳንቱ ቃል አቀባይ ቪንሰንት ማግዌንያ ራማፎሳ፤ የቀረበው የዲፕሎማሲ ደረጃ ለዝውውር ሥነ-ሥርዓቱ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለፅ የቡድን 20 ፕሬዝዳንትነትን ለአሜሪካ ጉዳይ አስፈፃሚ እንደማያስረክቡ ቀደም ሲል አረጋግጠዋል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0