ውጊያው መቀጠሉ ለዘለንስኪ እና ለአገዛዙ አደጋ ነው - የክሬምሊን ቃል አቀባይ
16:35 21.11.2025 (የተሻሻለ: 16:44 21.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ውጊያው መቀጠሉ ለዘለንስኪ እና ለአገዛዙ አደጋ ነው - የክሬምሊን ቃል አቀባይ
የዲሚትሪቭ ፔስኮቭ ቁልፍ መግለጫዎች፦
በግጭቱ ዙሪያ የኪዬቭ ሁኔታ፦
የሩሲያ ጦር ኃይሎች ውጤታማ ዘመቻ ዘለንስኪ እና አገዛዙን በይደር ከማቆየት አሁን መደራደር የተሻለ እንደሆነ ሊያስገነዝብ ይገባል፡፡
የሩሲያ ጦር ኃይሎች ግስጋሴ የዘለንስኪን የውሳኔ መስጫ ግዜ እያጠበበ ነው፡፡
ይህ ስለ ጦርነት ሳይሆን ዘለንስኪ እና አገዛዙን ወደ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲመጡ ስለመግፋት ነው፡፡
የኪዬቭ አገዛዝ አሁኑኑ ውሳኔ በመስጠት ኃላፊነት ሊወስድ ይገባል።
ስለ አሜሪካ የሰላም ዕቅድ የሚዲያ ዘገባዎችን በተመለከተ፦
ሩሲያ በአንኮሬጅ የተደረጉ ውይይቶችን መሠረት አድርጋ ቀጥላለች።
ሞስኮ የዩክሬን ጉዳይን ለመፍታት የተለያዩ ለውጦች እንዳሉ ታውቃለች ሆኖም በይፋ ምንም አልደረሳትም።
በሩሲያ እና በአሜሪካ መካከል ያለው ግንኙነት አልቆመም።
አሜሪካ በዩክሬን ሰላም ስምምነት ዙሪያ የራሷ አቋሞች አሏት ነገር ግን ተጨባጭ ውይይት እየተደረገ አይደለም።
ሩሲያ ለሰላማዊ ድርድር ዝግጁ ነች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X