በሩብ ዓመቱ 961 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል - የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን
16:23 21.11.2025 (የተሻሻለ: 16:24 21.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሩብ ዓመቱ 961 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል - የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን
ባለፉት ሶስት ወራት ከዘርፉ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ለመሳብ ታቅዶ እንደነበር ምክትል ኮሚሽነር ዳጋቶ ኩምቢ፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ተናግረዋል።
ለ123 የዉጭ ባለሀብቶች ፍቃድ መሰጠቱን የገለፁት ምክትል ኮሚሽነሩ፤ 34 የሚሆኑት በገቢና ወጪ ንግድ ላይ እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል፡፡
ኮሚሽኑ የኢንቨስትመንት ከባቢ ሁኔታን በማሻሻል የውጭ ባለሀብቶችን ለመሳብ በትኩረት እየሠራ እንደሚገኝም ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X