ሱዳናውያን አማጺው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለመመከት አገር አቀፍ ዘመቻውን እንዲቀላቀሉ ከፍተኛ አዛዡ ጥሪ አቀረቡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሱዳናውያን አማጺው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለመመከት አገር አቀፍ ዘመቻውን እንዲቀላቀሉ ከፍተኛ አዛዡ ጥሪ አቀረቡ
ሱዳናውያን አማጺው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለመመከት አገር አቀፍ ዘመቻውን እንዲቀላቀሉ ከፍተኛ አዛዡ ጥሪ አቀረቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.11.2025
ሰብስክራይብ

ሱዳናውያን አማጺው የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለመመከት አገር አቀፍ ዘመቻውን እንዲቀላቀሉ ከፍተኛ አዛዡ ጥሪ አቀረቡ

የብሉ ናይል የአየር መከላከያ ዘርፍ አዛዥ አሊ ሐሰን ቤሎ፣ ይህንን ጥሪ ያቀረቡት የሱዳን ጦር ኃይሎች ዋና አዛዥ አብደል ፈታሕ አል-ቡርሃን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች የሰሜን ዳርፉር ዋና ከተማ የሆነችውን አል-ፋሸርን ከተቆጣጠሩ በኋላ ሕዝቡ ድጋፍ እንዲያደርግ ላቀረቡት የቅርብ ጊዜ ጥሪ ምላሽ ነው።

የጦር አዛዡ ሱና በተባለው የመንግሥት ዜና ወኪል አማካኝነት ባስተላለፉት መግለጫ በኮርዶፋን ክልል የተገኙትን የቅርብ ጊዜ ወታደራዊ ስኬቶች አወድሰዋል።

“አሁንም በከበባ ውሰጥ ባሉ ከተሞች ድል አይቀሬ ነው” ሲሉ የሱዳን ወጣቶች የአል-ቡርሃንን ጥሪ እንዲቀበሉ አሳስበዋል።

ይህ የቅስቀሳ ዘመቻ የሚካሄደው ኡም-ሰያላን እና ሌሎች ስልታዊ ቦታዎችን ጨምሮ በበርካታ የኮርዶፋን አካባቢዎች ሠራዊቱ ድል ማድረጉን በሚያሳዩ ሪፖርቶች መካከል ነው።

ሠራዊቱ “አገሪቱ ከአመፅ እና ከውጭ አጀንዳዎች እስክትጸዳ ድረስ” በአማፂያኑ ላይ የሚያካሂደውን ዘመቻ እንደሚቀጥል ቃል ገብቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0