'በራሳቸው ፖሊሲ ተጠልፈዋል' - የአውሮፓ ሕብረት በሙስና ቅሌት ምክንያት ዘለንስኪን መተው አይችልም - የጂኦፖለቲኪና ደህንነት ተንታኝ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ'በራሳቸው ፖሊሲ ተጠልፈዋል' - የአውሮፓ ሕብረት በሙስና ቅሌት ምክንያት ዘለንስኪን መተው አይችልም - የጂኦፖለቲኪና ደህንነት ተንታኝ
'በራሳቸው ፖሊሲ ተጠልፈዋል' - የአውሮፓ ሕብረት በሙስና ቅሌት ምክንያት ዘለንስኪን መተው አይችልም - የጂኦፖለቲኪና ደህንነት ተንታኝ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.11.2025
ሰብስክራይብ

'በራሳቸው ፖሊሲ ተጠልፈዋል' - የአውሮፓ ሕብረት በሙስና ቅሌት ምክንያት ዘለንስኪን መተው አይችልም - የጂኦፖለቲኪና ደህንነት ተንታኝ

በቅርብ ጊዜ ውስጥ፣ የዘለንስኪ የ100 ሚሊዮን ዶላር ኃይል የሙስና ቅሌት አውሮፓውያን እንዲተዉአቸው ሊያደርግ አይችልም። ምክንያቱም "በዩክሬን ፕሮጀክት ላይ ትልቅ የፖለቲካና የፋይናንስ ኢንቨስትመንት" ማድረጋቸው ነው ሲሉ የጂኦፖለቲክስና ደህንነት ተንታኝ ዶ/ር ማርኮ ማርሲሊ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

"አሁን ዘለንስኪን መተው ስትራቴጂካዊ ውድቀትን እንደመቀበል ይቆጠራል፤ ለሞስኮም ቀጥተኛ ስጦታ እንደመስጠት ይታያል። በራሳቸው ፖሊሲ ተጠልፈዋል" ሲሉ ማርሲሊ አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

ተንታኙ አክለውም፣ "ሆኖም፣ በገሃድ የማይታይ ወሳኝ ለውጥ አስቀድመን እያየን ነው። የ 'ባዶ ቼክ' ፖሊሲ አብቅቷል። እነዚህ የሙስና ቅሌቶች የአውሮፓ ዋና ከተሞች የእርዳታ አቅርቦቶችን እንዲቀንሱ፣ ጥብቅ ሁኔታዎችን እንዲተገበሩ እና በቢሊዮን የሚቆጠሩ የገንዘብ ድጋፎቻቸው ውጤታማነት ላይ ጥያቄ እንዲያነሱ ምቹ አጋጣሚ ይሰጣቸዋል" ብለዋል።



ማርሲሊ እንደሚያስረዱት፣ የአውሮፓ ሚዲያዎች ዘለንስኪን ለመከላከል፣ ከቅሌቱ ለማራቅና እንደ "ፖለቲካዊ ሰለባ" አድርገው ለማሳየት የሚያደርጉት ጥረት "የታሪክ ትርክትን ለመጠበቅ የሚደረግ ወሳኝ ጉዳይ" ነው።

ተቃራኒውን ማድረግና እሳቸው "ዴሞክራት፣ የነጻነት ታጋይና... የምዕራባውያን እሴቶች ምልክት እንዳልሆኑ መቀበል የሚያሳፍር  ግምገማ እንዲካሄድ" ያስገድዳል፤ ይህም መንግሥቶቻቸው ለዩክሬን የሰጡትን "እጅግ ከፍተኛ የፋይናንስና ወታደራዊ ድጋፍ የሞራል ማረጋገጫ ሙሉ በሙሉ" ያዳክማል።

በሌላ አገላለጽ፣ "ዘለንስኪን መከላከል" ማለት የአውሮፓውያንን "የራሳቸውን ትርክትና የመንግሥታቸውን የውጭ ፖሊሲ ተዓማኒነት" መከላከልም ጭምር ነው ሲሉ ማርሲሊ አስምረውበታል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0