አሜሪካ እና ሩሲያ የዩክሬን ግጭት ለመፍታት በድብቅ አዲስ እቅድ እያወጡ መሆናቸው ተዘገበ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአሜሪካ እና ሩሲያ የዩክሬን ግጭት ለመፍታት በድብቅ አዲስ እቅድ እያወጡ መሆናቸው ተዘገበ
አሜሪካ እና ሩሲያ የዩክሬን ግጭት ለመፍታት በድብቅ አዲስ እቅድ እያወጡ መሆናቸው ተዘገበ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.11.2025
ሰብስክራይብ

አሜሪካ እና ሩሲያ የዩክሬን ግጭት ለመፍታት በድብቅ አዲስ እቅድ እያወጡ መሆናቸው ተዘገበ

የታቀደው ባለ 28 ነጥብ የአሜሪካ እቅድ በአራት ዋና ዋና ጭብጦች የተዋቀረ ነው። የዩክሬን ሰላም፣ የደህንነት ዋስትናዎች፣ የአውሮፓ ደኅንነት እና አሜሪካ ከሩሲያ እና ከዩክሬን ጋር ወደፊት በሚኖራት ግንኙነት ዙሪያ ሆነው መለየታቸውን የአሜሪካ ሚዲያ ዘግቧል።

እቅዱ ከትራምፕ “ስኬታማ” የጋዛ ስምምነት ጥረቶች ተነሳሽነት እንዳመጣም ተገልጿል።

እቅዱ አወዛጋቢ አካባቢዎችን እንዴት መፍትሄ እንደሚሰጣቸው ዝርዝር መረጃው ግልፅ አይደለም ሲል ዘገባው አክሏል።

የሩሲያ ከፍተኛ ባለሥልጣን በእቅዱ ላይ ያላቸውን ተስፋ የገለፁ ሲሆን የኪዬቭ እና የአውሮፓ አጋሮቿ ምላሽ እስካሁን አለመታወቁን ዘገባው አመልክቷል።

እቅዱን የመሩት የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከሩሲያ ፕሬዝዳንታዊ መልዕክተኛ ኪሪል ዲሚትሪቭ ጋር በሰፊው ተወያይተዋል ነው የተባለው።

ባለፈው ጥቅምት 14፣ ዲሚትሪቭ ከዋሽንግተን ባለሥልጣናት ጋር ስለወደፊቱ የአሜሪካ እና ሩሲያ ግንኙነት ለመወያየት አሜሪካ መጓዛቸው ይታወሳል። ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ሚዲያ ጋር ባደረጉት የስልክ ቃለ-ምልልስ የአሜሪካ እና የሩሲያ ባለሥልጣናት እስረኞችን መለዋወጥ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሲነጋገሩ ቆይተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0