“በ1920ዎቹ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ 12 ውድ ቅርሶች ወደ አገራቸው ተመልሰዋል” - የቱሪዝም ሚኒስትር
19:02 19.11.2025 (የተሻሻለ: 19:14 19.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
“በ1920ዎቹ ከኢትዮጵያ የተወሰዱ 12 ውድ ቅርሶች ወደ አገራቸው ተመልሰዋል” - የቱሪዝም ሚኒስትር
ፕሮፌሰር ራሞን ዊስ አያታቸው ከ100 ዓመት በፊት በአዲስ አበባ የጀርመን ልዑክ ሆነው በቆዩባቸው ዓመታት በስጦታና በግዢ አሰባስበው ያቆዩአቸውን ቅርሶች ዛሬ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት እና ምርምር ተቋም ማስረከባቸውን ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ አስታውቀዋል።
“የፕሮፌሰር ራሞስ ቤተሰብ፣ ቅርሶቹን ጠብቆ በማቆየትና አሁንም ወደ አገራቸው በመመለስ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር በተግባር ገልፀዋልና ላመሰግናቸው እወዳለሁ።”
ዛሬ ከተበረከቱት ውድ ቅርሶች ውስጥ ዘውዶች፣ ጋሻዎች፣ ጎራዴ፣ ዝናር፣ ሥዕሎች እንዲሁም ከራስ ተፈሪ መኮንን የተበረከቱ ስጦታዎች ይገኙባቸዋል ተብሏል፡፡
በመላው ዓለም በግለሰቦች እጅ እና በተቋማት ውስጥ የሚገኙና የኢትዮጵያ ታሪክ አስረጂ የሆኑ ጥንታዊ ቅርሶች ወደ አገር እንዲመለሱ የማድረጉ ጥረትም ይቀጥላል በማለት በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



