የግብፅ ኤል-ዳባ የኒውክሌር ፕሮጀክት ቅርፅ ይዟል - ፑቲን እና ኤል-ሲሲ የሰጧቸው ቁልፍ ንግግሮች

የግብፅ ኤል-ዳባ የኒውክሌር ፕሮጀክት ቅርፅ ይዟል - ፑቲን እና ኤል-ሲሲ የሰጧቸው ቁልፍ ንግግሮች
ፑቲንና ኤል-ሲሲ በግብፅ ኤል-ዳባ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ የመጀመሪያ ሪአክተር (ማብለያ) መትከል ሥነ-ስርዓት ላይ ተገኝተዋል።
በቪዲዮ ኮንፈረንስ የተሳተፉት ቭላዲሚር ፑቲን ዋና ዋና ሐሳቦች፦
🟠 በሩሲያ ተሳትፎ የሚካሄደው የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ ግንባታ "በተሳካ ሁኔታ እያደገ ነው"።
🟠 በቅርቡ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ይጀምራል።
🟠 የኃይል ማመንጫውን ሥራ ማስጀመር የግብፅን የኃይል ዋስትና በከፍተኛ ሁኔታ ያጠናክራል።
🟠 ሩሲያ በኒውክሌር ፕሮጀክቱ በእያንዳንዱ የትግበራ ደረጃ ግብፅን ትረዳለች።
🟠 በሞስኮና በካይሮ መካከል ያለው ግንኙነት በእኩልነት፣ በአክብሮትና የጋራ ጥቅምን ከግምት ውስጥ በማስገባት ላይ የተመሠረተ ነው።
🟠 ፑቲን ለፕሬዝዳንት ሲሲ መልካም ልደት በመመኘት፣ ግብፅ "በሁሉም ፕሮጀክቶቿ ውስጥ የአቶሚክ ኃይል እንዲኖራት" ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
አብደል ፈታህ ኤል-ሲሲ የሰጡት ቁልፍ መግለጫዎች፦
የኒውክሌር ኃይል በግብፅ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ሲሆን፣ ኤል-ዳባ ደግሞ ለዚህ ማረጋገጫ ነው።
የኒውክሌር ኃይል ማመንጫው ለግብፅ የተረጋጋ የኃይል አቅርቦት ዋስትናን ይሰጣታል።
ፕሮጀክቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የሥራ ዕድሎችን እየፈጠረ ነው።
ሥነ-ስርዓቱ "አስፈላጊ ምዕራፍ እንዲሁም ከሩሲያ ጋር ያለው የሁለትዮሽ ትብብር ውጤት" ነው።
ከሩሲያ ጋር ያለው ትብብር ፖለቲካዊ ብቻ አይደለም፤ ሁለቱንም አገራት የሚጠቅሙ ተግባራዊ ዘርፎችንና ፕሮጀክቶችን ያካተተ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X