ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች ኤክስፖርት ግንባር ቀደም ለመሆን እየጣረች ነው - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
16:32 19.11.2025 (የተሻሻለ: 16:34 19.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች ኤክስፖርት ግንባር ቀደም ለመሆን እየጣረች ነው - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ፣ ባለፈው የበጀት ዓመት አገሪቱ ወደ ወጭ ከላከችው ጥራጥሬና ቅባት እህሎች ከ610 ሚሊዮን ዶላር በላይ በማስገኘት 7.35 በመቶ ድርሻ እንደነበራቸው በ14ኛው ዓለም አቀፍ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች ጉባኤ ላይ አብራርተዋል።
ሚኒስትሩ ዘርፉ ያለውን ያልተነካ አቅም ከፍ ለማድረግ ከተወሰዱት ቁልፍ ማሻሻያዎች መካከል የሚከተሉትን ጠቅሰዋል።
የውጭ ባለሀብቶች ወደ ገበያ እንዲገቡ መፍቀድ፣
በገበያ የሚመራ የምንዛሬ ተመን መከተል እንዲሁም
ለተጨማሪ እሴትና በግብርና-ማቀነባበሪያ ላይ ትልቅ ትኩረት መስጠትን ያጠቃልላሉ ብለዋል፡፡
የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ) የቦርድ ሰብሳቢ የቀደሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ አነስተኛ አርሶ አደሮች ጥራጥሬና ቅባት እህሎችን በማምረት ለአገሪቱ ኢኮኖሚ አስተዋፅኦ እያደረጉ መሆናቸውን ተናግረዋል ሲል የአገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X