የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ግዙፉ ኤ350 አንቀሳቃሽነት ቦታውን የሚያጠብቁለትን 6 ኤ350-900ኤስ ኤርባስ አውሮፕላኖችን አዘዘ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ግዙፉ ኤ350 አንቀሳቃሽነት ቦታውን የሚያጠብቁለትን 6 ኤ350-900ኤስ ኤርባስ አውሮፕላኖችን አዘዘ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ግዙፉ ኤ350 አንቀሳቃሽነት ቦታውን የሚያጠብቁለትን 6 ኤ350-900ኤስ ኤርባስ አውሮፕላኖችን አዘዘ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.11.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ግዙፉ ኤ350 አንቀሳቃሽነት ቦታውን የሚያጠብቁለትን 6 ኤ350-900ኤስ ኤርባስ አውሮፕላኖችን አዘዘ

ስምምነቱን በዱባይ የአየር ትርዒት ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው እና የኤርባስ የንግድ አውሮፕላኖች ቢዝነስ ሽያጭ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳንቴ ኤግዡፔሪ ተፈራርመዋል፡፡

“እንደ አኅጉሪቱ መሪ አየር መንገድ እና ትልቁ የኤ350 አንቀሳቃሽ እንደመሆናችን፣ ይህ ወሳኝ ትዕዛዝ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የጉዞ ልምድ እየሰጠን እና በአፍሪካ የአቪዬሽን መሪነት ቦታችንን በማጠናከር በዘላቂነት የማደግ ርዕያችንን ይደግፋል።” ማለታቸውን አየር መንገዱ ድረ-ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ አስነብቧል፡፡

ሳንቴ ኤግዡፔሪ በበኩላቸው፣ ከነባር የኤርባስ ደንበኛቸው እና በአፍሪካ የአቪዬሽን ልህቀት ምሳሌ ከሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ያላቸውን አጋርነት የበለጠ በማጠናከራቸው ኩራት እንደሚሰማቸው ገልፀዋል፡፡

አዲሱ ትዕዛዝ አየር መንገዱ አውሮፕላኖቹን በቴክኖሎጂ ልህቀት፣ በነዳጅ ቆጣቢነት እና በአካባቢ ተስማሚነት ለማዘመን እና ለማስፋፋት ያለውን የረዥም ጊዜ ስትራቴጂ የሚያጎላ መሆኑ በመግለጫው ተገልጿል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0