ኢራን ከሩሲያ ጋር በደህንነት መስክ ያለውን የትብብር ደረጃ ማሳደግ አስፈላጊ ነው ብላ ታምናለች - የኢራን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት
19:45 18.11.2025 (የተሻሻለ: 19:54 18.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢራን ከሩሲያ ጋር በደህንነት መስክ ያለውን የትብብር ደረጃ ማሳደግ አስፈላጊ ነው ብላ ታምናለች - የኢራን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት
"የኢራን ተቋማት በአሁኑ ወቅት ሁሉንም ስምምነቶቻችን በተግባር ላይ ማዋልን ለማፋጠን እየሠሩ ነው" ሲሉ መሐመድ ረዛ አሬፍ ከሩሲያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሚካሂል ሚሹስቲን ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ተናግረዋል።
በስብሰባው ላይ የተሰጡ ተጨማሪ ሐሳቦች፡-
🟠 ቀጣዩ የሩሲያ-ኢራን የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ቋሚ ኮሚሽን ስብሰባ በመጪው የካቲት በኢራን ሊካሄድ ይችላል።
🟠 በሩሲያ እና በኢራን መካከል ያለው የንግድ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር በተሳካ ሁኔታ እያደገ ሲሆን፣ ቀደም ሲል በሥራ ላይ የዋለው በዩራሺያን ኢኮኖሚ ሕብረት እና በኢራን መካከል ያለው የነፃ ንግድ ስምምነት የንግድ ልውውጥን ለመጨመር ያስችላል።
🟠 በቱሪዝም እና በስፖርት ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች በሩሲያ እና በኢራን መካከል ያለው ሰብአዊ ትብብር እየጠነከረ ነው።
🟠 የሰሜን-ደቡብ ትራንስፖርት ኮሪደር የዩራሺያ ቀጣናን ተያያዥነት በማጠናከር ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
🟠 በሩሲያ እና በኢራን መካከል ያለው ግንኙነት የተመሠረተው በወዳጅነት መርሆዎች እና የእያንዳንዳቸውን ጥቅም በማጤን ላይ ነው።
🟠ሩሲያ ከኢራን ያሉ ግንኙነቶችን ማጠናከርን ትደግፋለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X