ኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር የኢትዮጵያን የቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በቅርቡ ለማስጀመር 340 ሚሊዮን ዶላር በጀት ማግኘቱን አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር የኢትዮጵያን የቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በቅርቡ ለማስጀመር 340 ሚሊዮን ዶላር በጀት ማግኘቱን አስታወቀ
ኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር የኢትዮጵያን የቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በቅርቡ ለማስጀመር 340 ሚሊዮን ዶላር በጀት ማግኘቱን አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 18.11.2025
ሰብስክራይብ

ኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር የኢትዮጵያን የቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በቅርቡ ለማስጀመር 340 ሚሊዮን ዶላር በጀት ማግኘቱን አስታወቀ

በኢትዮጵያ በምዕራብ ወለጋ ቱሉ ካፒ አካባቢ የሚተገበረው ፕሮጀክቱ ቁልፍ የፋይናንስ ምንጮችን ማስጠበቅ እና ከፕሮጀክቱ አጋሮች ጋር ስምምነት ላይ ከደረሰ ከ2019 ዓ.ም አጋማሽ በፊት ግንባታ ለመጀመር ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።

ድርጅቱ ለከፍተኛ ደረጃ የወርቅ ክምችቱ ያዘጋጀው ሙሉ የልማት ዕቅድ በፋይናንስ ሰጪዎቹ ቡድን መፅደቁ የተገለጸ ሲሆን ይህም ለመጨረሻው የፋይናንስ ስምምነት መደምደሚያ መንገድ ከፍቷል።

ድርጅቱ የአገር ውስጥ የግልና የመንግሥት ባለሀብቶችን በአገር ውስጥ ገንዘብ ለማሳተፍ እየተዘጋጀ ሲሆን፣ ለወደፊት በኢትዮጵያ የኩባንያውን ቅርንጫፍ በገበያ ላይ ለመሸጥ የሚያስችል መሠረት እየጣለ መሆኑ ሚዲያ ዘግቧል።

የፕሮጀክቱን ቁርጠኝነት የሚያመለክቱ ስምምነቶች ከፌዴራልና ክልል ባለሥልጣናት፣ ከአበዳሪዎች፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊ የሀብት ፈንድ፣ ከአገር ውስጥ ተቋራጮች እና በፕሮጀክቱ የበጎ አድራጎት ድርጅት መካከል ተፈርሟል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0