ኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር የኢትዮጵያን የቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በቅርቡ ለማስጀመር 340 ሚሊዮን ዶላር በጀት ማግኘቱን አስታወቀ
18:48 18.11.2025 (የተሻሻለ: 18:54 18.11.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር የኢትዮጵያን የቱሉ ካፒ የወርቅ ፕሮጀክት በቅርቡ ለማስጀመር 340 ሚሊዮን ዶላር በጀት ማግኘቱን አስታወቀ
በኢትዮጵያ በምዕራብ ወለጋ ቱሉ ካፒ አካባቢ የሚተገበረው ፕሮጀክቱ ቁልፍ የፋይናንስ ምንጮችን ማስጠበቅ እና ከፕሮጀክቱ አጋሮች ጋር ስምምነት ላይ ከደረሰ ከ2019 ዓ.ም አጋማሽ በፊት ግንባታ ለመጀመር ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
ድርጅቱ ለከፍተኛ ደረጃ የወርቅ ክምችቱ ያዘጋጀው ሙሉ የልማት ዕቅድ በፋይናንስ ሰጪዎቹ ቡድን መፅደቁ የተገለጸ ሲሆን ይህም ለመጨረሻው የፋይናንስ ስምምነት መደምደሚያ መንገድ ከፍቷል።
ድርጅቱ የአገር ውስጥ የግልና የመንግሥት ባለሀብቶችን በአገር ውስጥ ገንዘብ ለማሳተፍ እየተዘጋጀ ሲሆን፣ ለወደፊት በኢትዮጵያ የኩባንያውን ቅርንጫፍ በገበያ ላይ ለመሸጥ የሚያስችል መሠረት እየጣለ መሆኑ ሚዲያ ዘግቧል።
የፕሮጀክቱን ቁርጠኝነት የሚያመለክቱ ስምምነቶች ከፌዴራልና ክልል ባለሥልጣናት፣ ከአበዳሪዎች ፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊ የሀብት ፈንድ፣ ከአገር ውስጥ ተቋራጮች እና በፕሮጀክቱ የበጎ አድራጎት ድርጅት መካከል ተፈርሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X