የአውሮፓ ሕብረት በታገዱ የሩሲያ ሀብቶች ላይ ያለው ማመንታት በኪዬቭ ላይ ያለው እምነት እየቀነሰ መሄዱን አመላካች ነው - ዘገባዎች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአውሮፓ ሕብረት በታገዱ የሩሲያ ሀብቶች ላይ ያለው ማመንታት በኪዬቭ ላይ ያለው እምነት እየቀነሰ መሄዱን አመላካች ነው - ዘገባዎች
የአውሮፓ ሕብረት በታገዱ የሩሲያ ሀብቶች ላይ ያለው ማመንታት በኪዬቭ ላይ ያለው እምነት እየቀነሰ መሄዱን አመላካች ነው - ዘገባዎች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 18.11.2025
ሰብስክራይብ

የአውሮፓ ሕብረት በታገዱ የሩሲያ ሀብቶች ላይ ያለው ማመንታት በኪዬቭ ላይ ያለው እምነት እየቀነሰ መሄዱን አመላካች ነው - ዘገባዎች

ሕብረቱ ከታገዱ የሩሲያ ሀብቶች 140 ቢሊዮን ዩሮ የመጠቀም ወይም ያለመጠቀም ውሳኔውን በተደጋጋሚ ማራዘሙ ከሕግ ወይም ከፋይናንስ ጋር የተያያዘ ቴክኒካዊ ጉዳይ ብቻ አይደለም ተብሎ እየታየ ነው።

ዘ ኮንቨርዜሽን ባቀረበው ዘገባ መሠረት፣ ይህ መዘግየት ጥልቅ የሆነ ስልታዊ ለውጥ የሚያሳይ ነው፡ አንዳንድ የአውሮፓ ሕብረት መሪዎች ዩክሬን በጦር ሜዳ ላይ ልታሸንፍ እንደምትችል ያላቸው እምነት የቀነሰ ይመስላል።

በይፋ፣ ብራስልስ የሕግ አደጋዎችን ጠቅሳለች፣ ሊከሰቱ የሚችሉ ክሶችን እና በተለይም ከ200 ቢሊዮን ዩሮ በላይ የሚሆነው የሩሲያ የታገደ መጠባበቂያ በቤልጂየም ዩሮክሊር ውስጥ የሚገኝ በመሆኑ የአውሮፓ ሕብረት የፋይናንስ መልካም ስሙን ስለሚመለከት ያሳስበኛል ብላለች።

ካለፈው ጥር እስከ መስከረም ባለው ጊዜ ውስጥ፣ የአውሮፓ ሕብረት ከእነዚህ ሀብቶች የተገኘውን 14 ቢሊዮን ዩሮ ገቢ ለዩክሬን አስተላልፏል፤ ነገር ግን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ማድረጉ ላይ ዘግይቷል።

ሞስኮ “ወንጀለኛ ጠባይ” ብላ የምትጠራው ማንኛውም “የማካካሻ ብድር” ዕቅድ እንዲሁም ሩሲያ የአጸፋ እርምጃዎች ለመስጠት የገባችውን ቃል በመገንዘብ፣ ቤልጂየም የተጠያቂነት ከለላን እየፈለገች ነው ተብሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0